Skip to content
Saturday, 02 September 2017 12:02
ለታላቁ የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲ የሚሾመው ማነው?
የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንትነት: ጥሪ፥ ችሎታ ወይስ ሹመት?
-
“ከማይኾን ሹመት የሚመነጭ እኩይ ፍሬን እንደማየት አስከፊ ነገር የለም፡፡ በአንጻሩ፥ ችሎታ ያለው፣ ሠናይ እና ፍትሐዊ የኾነ ሰው በቦታው ላይ ሲሠየም እንደማየት በእጅጉ ደስ የሚያሰኝ ነገር የለም፡፡” (ቻርለስ ደብሊው ኤሊየት፣ ሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ 1869)
-
ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ
የአድማሱ ጸጋዬ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንትነት መነሣት፣ ለተቋሙ እንደ አንድ ትልቅ ዕድል ተደርጎ በብዙዎች ዘንድ ተወስዷል፡፡ ይኹን እንጂ፣ በቅርቡ በየብዙኃን መገናኛው በሰፊው እንደተሰማውና፣ በፓርላማ ፊት የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ባቀረበው፣ “የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ2007 በጀት ዓመት የኦዲት ግኝት ሪፖርት ውጤት” መሠረት፣ በዩኒቨርሲቲው ከፍ ያለ የፋይናንስና የንብረት አያያዝ ችግሮች በመገኘታቸው፣ የቀደሙት ዐሥር ያህል ዓመታት ተጨማሪ ምርመራ ማድረግ አስፈልጎ፣ ከውጪ ልዩ ኦዲተር ተሠይሞ፣ በምርመራ ላይ ባለበት በዚህ ወቅት፤ እኛም እንደ ዜጋ፤ “የዐቃቤ ሕግ ያለህ!” እያልን በምጮንህበት በዚህ ሰዓት፣ መንግሥት ፕሬዝዳንቱን “አምባሳደር” ብሎ በመሾም ከዐይን እንዲርቁ ማሸሹ፣ ብዙ ቁጭት እና ንዴት ቀስቅሷል፡፡ ይህ ድርጊት ከሞራል አንጻር ሓላፊነት የጎደለው ውሳኔ ይመስላል፡፡
- ለማንበብ(PDF)ይህን ይጫኑ⇓
- https://ethiopanorama.comwp-content/uploads/2017/09/Dangachew.pdf
Like this:
Like Loading...