በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ እንደ ትግራይ ነፃ አውጭው ግምባር የወንበዴ ቡድን ያሰበውን ያሳካ የለም፡፡

የተከዜ ማዶ ነፃ አውጭ የወንበዴው ቡድን፤የስልጣን ጥመኞች እና ነብሰ በላው ወታደራዊ አገዛዝ የመከራ ቀን ሰልፈኞች ጥርቅም ታላቋን ትግራይ ለመመስረት ያለውን ፍላጎት ለማሳካት ኢትዮጵያ የምትባለውን ሀገር እጅ እግሯን አስሮ፤ወገቧን አጉብጦ የቁም እስረኛ ካደረጓት ሶስት አስርተ አመታት ቢጠጉም ለሀገር ወዳዱ ሀገር አልባ ህዝብ ግን ያሳዝናል፡፡ የተከዜ ማዶ ሽፍቶች ታላቋን ትግራይ ለመመስረትም የአማራ ለም መሬቶችን መዝረፍና የኢትዮጵያን ድንበርም ሉዓላዊነቷን አሳልፎ መስጠት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡


በተከዜ ማዶ አምባገነኖች የስልጣን ዘመን ይህ ሆነ፦
1-የትግራይ ክልል ለዘመናት ተራቁቶ የነበረው አካባቢውን መልሶ ለማልማት ባወጣው ፖሊሲና ባደረገው ጥረት ለተገኘው ውጤት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳድሮ አንደኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ለመሆን መብቃቱን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በረሀማነት እንዳይስፋፋ የሚሠራ ቢሮ የገለፀ ሲሆን። ልማቱ ላይ ተቃውሞ ባይኖረኝም ታላቋ ትግራይ የምትባለው የኢትዮጵያ ጎረቤት ሃገር ከሌሎች የአለም ሃገራት ጋር ከሆነ እንግዲህ ውድድሩ በርግጥ በድርቅ ምክንያት 10 ሚሊዮን የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ እርዳታ የሚፈልገው የኢትዮጵያ ህዝብ ለተከዜ ማዶ አምባገነኑ አይመለከትም ማለት ነው ምክንያቱም ሽልማቱን ለማሳየት የተጠቀመበት ካርታ ትክክለኛው የትግራዩ ነፃ አውጭ ግንባር የመሰረተውን እና እየመሰረተ ያለውን የታላቋን ትግራይ ካርታ እና ከአማራ ክልል የተወሰዱ መሬቶችን በግልጽ አሳይቶናል ይህም ወያኔ ከተመሰረተበት የደደቢት በርሃ እና ከማህበረ ገስገስቲ ትግራይ ጀምሮ ሟቹ ባለራእይ የተንኮል ሊቅ ያቀደውን ካርታ እንዳሳካ በልማታዊ ሚዲያው ሲያሳየን የህዝቡን ትርታ ለማወቅ እንጅ ያለቀ ካርታ እንደሆነ ሁሉም የሚያውቀው ጉዳይ በመሆኑ ታላቋ ትግራይም ሽልማቱን እንደሃገር አሸንፋለች፡፡

* ከዚህም በተጨማሪ በአቢጃታ ሃይቅ በተከሰተው ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋ እንዲሁም ድርቅ ምክንያት ከነበረው 100 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ውስጥ 50 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ደርቆ ልጆች ድሮ ሃይቅ በነበረው ቦታ ላይ ኳስ ሲጫወቱበት የተከዜ ማዶዎች ማፊያ መርዶ ነጋሪ የሆነው ኢቢሲ ዘግቦታል ሊንኩን ይጫኑ (https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1624508107581059&id=541629952535552)ታዲያ ይሄ ምን ማለት ነው? በአንድ ሃገር ውስጥ ብንሆን ኑሮ ይሄ ልዩነት ባልኖረ ነበር፡፡

***ሌላው ጉዳይም ጣና ሃይቅ እምቦጭ በሚባል መጤ አረም ሲወረር ህዝቡ ራሱን ሃይቁ ውስጥ አስገብቶ ለማጽዳት እየሞከረ ቢሆንም በተከዜ ማዶ ሰዎች እይታ ግን ለታላቋ ትግራይ ግንባታ ጥቅም የሌለው በመሆኑ እና የማይዘረፍ ሃብት በመሆኑ እንደ አቢጃታ ሃይቅ ሁሉ ጣና ሃይቅም እንዲደርቅ ወያኔ የበኩሉን እየሰራ ይገኛል፡፡ በጣም የሚገርመው ደግሞ ሃይቁ ያጋጠመውን አደጋ ለመታደግ ከህዝቡ ገንዘብ እየተሰበሰበ ስለመሆኑ እና አሁንም ሃይቁን የማዳን ስራ በህዝቡ ላይ እንጅ በተከዜ ማዶ ባለስልጣኖች ዘንድ ምንም ሃሳብ ውስጥ እንዳልገባ በኢቢሲ ድጋሚ ሰማን ሊንኩን ይመልከቱ(https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1634962746535595&id=541629952535552)

የደስታ መግለጫ፦ የምስራቅ አፍሪካ በየነ መንግስታት ለታላቋ ትግራይ እና ለተከዜ ማዶ የስልጣን ጥመኞች ሽልማቱን አስመልክቶ የደስታ መግለጫ ላከ የሚል ዜና ሰማን ወይ የጉድ ሀገር ለካ እኛ ሳናውቀው ታላቋ ትግራይ እንጅ ኢትዮጵያ አልነበረችም የኢጋድ አባል፥
ለካ በአለም አቀፍ መድረክ ኢትዮጵያ የምትወከለው በአዲሲቷ ሀገር በታላቋ ትግራይ ነው፡፡ የጉድ ሀገር ህዝቦች አቤት ስናሳዝን ሀገር ከአንድ ሰፈር ሲያንስ ይገርማል፡፡ ይህ ነበር የሟቹ ራእይ ለዚህም ነው ያሰቡትን አሳክተዋል ያልኩት፡፡

2ኛ-አሁንም ታላቋ ትግራይ ከአለም ሀገሮች ጋር ተወዳድራ የሲጋራ አጫሾችን ቁጥር በመቀነስ ከአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ሽልማቱን በአለም የጤና ድርጅት ካሸነፉ ሀገራት ውስጥ፦
1ኛ -የትግራይ ክልል
2ኛ -ጋምቢያ
3ኛ-ካሜሮን
4ኛ -ጋና
ዝርዝር ዜናው እዚህ ሊንክ ላይ ይገኛል(https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1395858750513482&id=907126906053338)ይህ እንግዲህ የትግራይ ሪፑብሊክን ለአለም የማሳወቂያ አንዱ ዘዴ ነው፡፡ አንድ ሀገር ውስጥ ብንሆን ኑሮማ የሚቀድመው ከሰፈር ስም የሃገር ስም ነበር፡፡ ግን እንዴት ነው ሌሎች ክልሎች የሲጋራ ፍብሪካ አላቸው እንዴ ያልተሸለሙት?

ይህ እንግዲህ ትግራይን እንደ ሃገር የማቆሙ ስራ ድብቅ ሳይሆን በግልፅ የአማራ ለም መሬቶችን በመዝረፍ እና በወያኔ የብሔረሰብ ጭምብል አዲስ የከፋፍለህ ግዛ መርህ እቅዱን አሳክቷል፡፡ ይህም መጀመሪያ የአማራ ክልልን በሱዳን በኤርትራ እና ጅቡቲ አዋሳኞችን መዝጋት ጀምሮ ነው፡፡

እንደሚታወቀው ከ1961 እስከ 1991 ድረስ የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ካበቃበት ከ1991 ጀምሮ እና ኤርትራም እንደ ሃገር ከቆመች ከ1993 ጀምሮ ወያኔም ጫካ ላይ የነበረውን ካርታ ተግባራዊ ማድረግ ጀመረ፡፡(ካርታ 1 ከ1991 በፊት የነበረው የአማራ ክልል ካርታ ይመልከቱ)በዚህ ካርታ ላይም የአማራ ክልል ከሱዳን ከኤርትራና ከጅቡቲ ጋር ያለውን የድንበር አዋሳኝ የሚያመላክት ሲሆን ካርታ 2 ላይ በግልጽ እንደሚታየውም ወሎ ሙሉ በሙሉ ከጅቡቲ ድምበር ባማውጣት እና በጎንደር በኩል ያለውን የኤርትራ ድምበር ለመዝጋት የተሞከረ ሲሆን አሁንም በሱዳን በኩል ያለውን አዋሳኝም ለመዝጋት ከአማራ ክልል የተዘረፉ ለም መሬቶችን በካርታ 3 ላይ ማየት ይቻላል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ አሁን ባለው የሰሜን ጎንደርን የመከፍፈል ሴራ የቅማንትን ህዝብ እንደመሳሪያ በመጠቀም የሱዳን ሰፊ አዋሳኝ የሆኑትን ቋራንና መተማን በብሔሩ ስም በማካተት አዲሲቷን ትግራይ የቤንሻጉል ለም መሬቶችን እና ሌሎች ድምበር ላይ ያሉትንም በመጨመር ሙሉ በሙሉ አማራ ክልልን ከሱዳን ድንብር የማጥፍቱ ስራ እየተሰራ መሆኑን ሰሞኑን ይቅርታ የተጠየቀበት ካርታ ማሳያ ነው፡፡

የሃገሪቱን የድምበር አዋሳኞችም በተለይ በሱዳን በኩል ያለውን መሬት ወያኔ ለሱዳን ለመስጠት የሚያደርገውን ጥረት እና የስጋት ቀጠና ብሎ የከለለውን ድምበር ገበሬው ከወያኔ ወታደር እና ከሱዳን ወታደር ጋር ጦርነት ከጀመረ አመታት ያለፉ ሲሆን ነገር ግን ሀገራዊ ትኩረት ባለማግኘቱ እና ድምበሩን የማስመለስና የማስከበር ሂደትም ክልላዊ ይዘት ተላብሷል ይህም የከፋፍለህ ግዛው መርህ በመስራቱ ነገም ቤንሻንጉልን በእድሜ ትንሿ መንግስት ደቡብ ሱዳን ጠቅልላ መውሰዷን ጉዳዩ ካለቀ በሗላ ልንሰማ እንችላለን ልክ ኢትዮጵያ የምትወከለው በታላቋ ትግራይ መሆኑን ከሰሞነኛ ሽልማቶች እንደሰማነው፡፡ ይህ ነው የሟቹም ራእይ፡

ሰሎሞን ይመኑ