ሙሉነህ ዮሐንስ
(ነሃሴ 30 2009) ቅማንትን ከአማራ ለመለየት ወያኔ ባወጀው የደባ ምርጫ ስም ለመስከረም 7 2010 ቀጠሮ ተይዞ ጎንደር እየታመሰች ነው።


ይህን እኩይ ተግባር ላማሳካት በቅማንት ስም የመራጭነት መታወቂያ የታደላቸው 5342 ተቀጣሪ በየቀበሌቹቸ ኗሪ ያልሆኑ ተወርዋሪ መራጮች ተዘጋጅተዋል። ይህ ህጋዊ በሆነ ምርጫ እንኳን ያሁኖቹ እጅግ በአብዛኛው አማራው የሚኖርባቸው 12 ቀበሌወች ቀርቶ በአንደኛው ዙር ያደረጉትም የሃሰት ምርጫ ምን ያክል ውንብድና እንደተሰራበትና ህዝቡ መከፋፈል እንደማይፈልግ ማረጋገጫ ነው። ይህም ዘላቂነት እንደማይኖረው ጥርጥር የለውም።


በተያያዘም ጉዳይ በቅማንት ስም አፈትልኮ የወጣው የወያኔ ሰነድ እንደሚያጋልጠው በምርጫ ቦርድ ስም የመጡት አስመራጮች ወያኔ የማይፈልገው ውጤት ከሆነ አዲስ ወረቀት የተሞሉ ኮራጆወች አዘጋጅተዋል እነሱን ይተካሉ።


ይህ እጅግ በወንጀል የታጨቀ የወያኔ ሰነድ በእቅዱ መሰረት አማራን ከቅማንት “ምድር” ለማፅዳት መወሰድ ስላለባቸው ደባወች በዝርዝር ተቀምጧል።
ይህንን እኩይ በቅማንትን ስም የመጣ የወያኔ አጀንዳ በማስፈፀም የጎንደር ዩንቨርስቲ በምሽግነት ተመርጧል።


ሰፊው የጎንደር ህዝብ ይህን እኩይ ተግባር ቀድሞ ቢውያቀውም በሰነድ ደረጃ በማስረጃ ስለተጋለጠ አፋጣኝ የአፀፋ እርምጃ እንደሚወሰድ ከስፍራው የሚደርሰን ሪፖርት ያመለክታል። በወንጀሉ እጃቸውን የከተቱ ሁሉ ለሚደርስባቸው ማንኛውም እርምጃ ተጠያቂወቹ እራሳቸውና አለቃቸው ወያኔ መሆኑን በአፅንኦት ተነግሯል።