Addis Ababa, September 19, 2017 :- We are disturbed by the troubling reports of ethnic violence and the large-scale displacement of people living along the border between the Oromia and Somali regions, particularly in Hararge, although the details of what is occurring remain unclear.

We urge the Ethiopian government to conduct a transparent investigation into all allegations of violence and to hold those responsible accountable.  At the same time, on the local level, communities must be encouraged and given space to seek peaceful resolutions to the underlying conflicts.

We believe Ethiopia’s future as a strong, prosperous, and democratic nation depends on open and inclusive political dialogue for all Ethiopians, greater government transparency, and strengthening the institutions of democracy and justice.  These recent events underscore the need to make more rapid and concrete progress on reform in these areas.

###

የአሜሪካ ኤምባሲ  በኦሮሚያ-ሶማሌ ድንበር የተከሰተውን የጎሳ ግጭት አስመልክቶ ያወጣው መግለጫ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 9፤ 2010 ዓ.ም. – በኦሮሚያ እና ሶማሌ አዋሳኝ አካባቢዎች በተለይም በሐረርጌ  የጎሳ ግጭትን እና የበርካታ ሰዎችን መፈናቀል አስመልክቶ በሚወጡ አሳሳቢ ዘገባዎች ተረብሸናል፤ ምንም እንኳ ዘገባዎቹ ስለሁኔታው ዝርዝር መረጃ ስለማቅረባቸው ግልጽ ባይሆንም፡፡

በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግሥት ግጭቱን ግልጽ በሆነ አካሄድ እንዲያጣራ እና አጥፊዎችን ተጠያቂ እንዲያደርግ እንጠይቃለን፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ፤ ግጭቱ በተከሰተባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ለችግሩ ሰላማዊ መፍትሔ እንዲሹ መበረታታት ይኖርባቸዋል፡፡

ኢትዮጵያ ጠንካራ፤ የበለጸገች እና ዴሞክራሲያዊት ሀገር መሆን የምትችለው፤ ግልጽና ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ውይይት፤ ግልጽ የመንግሥት አሰራር፤ እንዲሁም የዴሞክራሲ እና የፍትህ ተቋማትን ማጠናከር ስትችል እንደሆነ እናምናለን፡፡ የሰሞኑ ሁነቶች በተጠቀሱ ዘርፎች ይበልጥ ፈጣን እና ተጨባጭ ለውጥ አስፈላጊ እንደሆነ አመላካች ናቸው፡፡

Source    –    By | 19 September, 2017