♠ 4ቱ ቀንደኛ የህወሃት ጅምላ ተጠቃሚዎች!
♠ በርሄ፣ ገብረ አናንያ፣ ነጋሲ እና ገብረ ስላሴ
♠ በጎንደር ከተማ እጅግ የናጠጡ ሃብታሞች የሚባሉት ነጋሲና ገብረ አናንያ ናቸው!

ከአክቲቭስት ሙሉነህ ዮሐንስ

በርሄ እና ሽርካዉ ገብረ አናንያ፦
በርሄ እና ገብረአናንያ ዳንሻ፣ ሁመራ፣ ማይካድራ፣ እንዲሁም ወልቃይትን ጨምሮ የአረቂና የቢራ ጅምላ አከፋፋ ናቸው። ጃንተከል ዋርካ አካባቢ ብቸኛ የወይን አከፋፋይ፣ መቀሌ የሚመረት አረቂ ደስታ የሚባል መጠጥ አከፋፋዮች ናቸው።
በጣም የሚገርመው የአዋሽ ወይን እና ብሄራዊ አረቂ ብቸኛ ወኪሎች ትግሬ የህወሃት ሰወች ብቻ ናቸዉ። አንድ እማኝ ሲነግሩን “እኔ ነጋዴ ነኝ። ብዙ ታገልን። ነገር ግን ያለ ጨረታ ትግሬ ወያኔ ስለሆኑ ብቻ ያለ ተጫራች ይሰራሉ። እኛ በገዛ ሃገራችን የበይ ተመልካች ሆንን”። ይህ ግን ካሁን በኋላ በቃ ይላሉ የጎንደር ኗሪዎች። እነሱ ለአድልዎና ለመበደል ይሉንታ ከሌላቸው እኛም ለማጋለጥና ጥቅሞቻችንን ለማስመለስ ዝምታችን በቅቶታል ይላል ህዝቡ።

ነጋሲና ገብረ ስላሴ፦
ብቸኛ የብሄራዊ አከፋፋዩ ነጋሲ አረጋዊ ፔፕሲ አካባቢ ይገኛል። እኒህ ሁለቱ ቀንደኛ ወያኔወች የሚከተሉትን ምርቶች በሞኖፖል ተሰጥቷቸው በብቸኝነት እያከፋፈሉ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ያካብታሉ። ካምፓኒው የሆላንዶች ቢሆንም ለትግሬ ብቻ ነው የተፈቀደ በማለት በምሬት ይናገራሉ የጎንደር ነጋዴዎች።

የሄንከን ምርቶች ማለት፦
– ዋሊያ ቢራ
– ሃረር ቢራ
– ሄንከን ቢራ
– የበደሌ ቢራ
– የዋሊያ ራድለር ቢራ
– ሶፊ ማልት
– በክለር ቢራ

ጎንደር ከተማን እሰከ ቀሃ ወንዝ ድልድይ የሄንከን ምርቶችን በጅምላ ያከፋፍላል ይህ ነጋሲ።

ከጭልጋ፣ ነጋዴ ባሀር፣ መተማ፣ ቋራ፣ ድረስ የሄንከን ምርቶችን በጅምላ ያከፋፍላሉ። ነጋሲና ገብረ ስላሴ ሁለቱ የህውሃት ቁንጮ ናቸው። ከዚህ ቀደም ጎንደር ከተማ ቦንብ በነጋሲ መኖሪያ ቤት ተወርውሮ መኪና ተጎድቶ ነበር። ገ/ሰላሴ ደግሞ በሐምሌ ወር 2008 በነበረው ህዝባዊ ተቃውሞ ከሆቴሉ (ሮማን ሆቴል) ፎቅ በመውጣት አንድ ግለሰብ በጥይት ማቁሰሉ ተገልጿል። ነጋሲ በመዘበረው ገንዘብ በማናለብኝነት ጎንደር ከተማ ቀበሌ 13 ፔፕሲ አጠገብ ግዙፍ ፎቅ እየገነባ ይገኛል።

መረጃውን አጠናቅረው ከጎንደር ላደረሱን እያመሰገንን የማጋለጡን ስራ በይበልጥ እንገፋበታለን!