October 5, 2017 18:00

መግቢያ

ለ26 አመት አላላውስ ብለው ጨምቀው የያዝዋት በኢትዮጵያ ገላ የተጠመጠሙት ከጫካ የወጡ አስደንጋጭ የደራጎን እባቦች፤ የመጨረሻውን መርዛቸው በመርጨት ላይ ናቸው። በደራጎኖቹ ላለመነደፍ ሁሉም በሩቅ እየሸሸ ነው። የገዳማት፤ የቤተክርስትያንና የመስጊዶቿ በሮች ሁሉ ተበረጋግደው በሚያሳዝን ሁኔታ አጋንንቶቹ ተቆጣጥሮዋቸዋል፤ ፈጣሪዋም አገር ጥሎ ሄዷል። አማልክቶቿም በብርቱ ሐዘን ላይ ተቀምጠዋል። በምናኔ የሚኖሩ ቅጠል እየበሉ ከእግዚአብሔር ጋር በፀሎት የሚገናኙ የገዳማት አንስት መኖክሲቶች በአጋንንቶቹ መደፈራቸው ነግረውናል። አግዚኦ ተሳሃለነ!!

ላለመሞት ትንፈራገጣለች፤ ደራጎኖቹ ግን አልለቅ ብለው ጨምቀው ሊገድልዋት ይታገላሉ። ልጆቿ ከአጽናፍ አጽናፍ ተደናግጠዋል። አንዳንዶቻችን ከተመደብንበት ከመከላከያው የቀጠና ሰረገላ ወርደናል። ምን እየተደረገ እንደሆነም አናውቅም። አገራችን ጊዜ በሰጣቸው ትግሬዎች እየታመሰች ነች። እናቶቻችን፤ እህቶቻችን፤ ወንድሞቻችን፤ ዜጎቻችን ተደፍረዋል። ደጋግ ሰዎች ያለማቋረጥ ወደ ጭለማ ክፍል እየተገፈተሩ ነው። ይሙቱ ይታሰሩ ይደብደቡ ይዋረዱ እኛን አስካልነካን ጉዳያችን አይመስልም። ለማወቅም ፍላጎት አላሳየንም። ነቢቦቻችን ተለቅመው ጠፍተዋል። የቀሩትም የማያፈሩ የበሰበሱ ዕጽዋት ሆነዋል። 26 አመት ሙሉ ‘ክፉም ሆነ ደግ ሰው መርዝ ሰጪ የሆነበት፤ እገሌ ከእገሌ ሳይባል ማንኛውም ሰው ማንነቱን የሚያጣበት፤ ሰው ሁሉ ቀስ በቀስ ራሱን መግደል የያዘበት አገር ተችሮልናል’። ሰዎች የመሆን ባሕሪ ጥለው ወደ ድራጎን እና አጋንንትነት የተለወጡት የትግራይ ወያኔዎች አገሪቷን እያስጨነቁዋት ናቸው። ገበያ ላይ ወርደው የሚሸጡት ብቀላቸውና ክፋታቸው እንደ ፍም እሳት ይንቀለቀላል። ከገበያቸው ለመሸሽ ስንሞክር መላ ቅጡ ጠፍቶን ለረዢም ጊዜ በጭለማው መደናበሩን አማራጭ አድርገን ይዘነዋል። እናት በልጇ ሬሳ ተቀምጣ የረዳት ያለህ ታለቅሳለች። ፍርሐታችን አንደኛውን እግራችን አስበልቶ ሁለተኛውን እግራችንም ለመበላት እያመቻቸላቸው ነው። እስከመቸ?

ኢትዮጵያ ለ26 አመት ሞት፤ ስደት፤ ውርደት፤ አመጽ፤ እንግልት፤ እስራት፤ ድብደባ፤ ጦርነት፤ ግድያ፤ ዘረፋ፤ ክሕደት፤ግብረሰዶማዊ ዝሙት በተዘጋጀላት ሞገደኛ’ማዕበል ውስጥ ገብታ ትንገላታለች። ትዕቢት ባሳበዳቸው ብሔራዊ ስሜት በራቃቸው ‘የቀወሱ’ ሰዎች የአገራችን ሕይወት ሸምቀው ይዘውታል። ባዘጋጇቸው የጭለማ እስርቤቶች እርግብ ወጣት ሴቶችን መድፈር ሳያንሳቸው ተባዕትም ጭምር  ይደፍራሉ። አውላላ ሜዳላይ በቆሙ የኢትዮጵያ ሸበላ ወጣቶች ከሰማዩም ከፎቁም ጥይት ያዘንቡባቸዋል፤ በእያሪኮ ጩኸት እስከ መቸ?

በለስ ቀንቷቸው ይህ ሁሉ ሽብር የሚያካሂዱብን የወያኔ ትግሬዎች የመጡበት ክፍለሃገር’ እኔም ከተወለድኩበት ክ/ሃገር ነው። ብዙዎቹ መሪዎች በትምህርት ወይንም በትውውቅ ወይንም በጉርብትና በጓደኝነት፤ አስቀድሰን ተጫውተን ስቀን፤ በቅርብ የምንተዋወቅ አብሮ አደግ ነን። እንዲህ ያለ አስደንጋጭ ዘመን ያመጣሉ ብየ ገምቼ አላውቅም። እንዴት ተከሰተ? እንዴትስ ተዳራጁ? ሰምታችኋቸው የማታውቋቸው አዳዲስ ታሪኮችና ስለ ትግራይ ሕዝብ በየደረጃው በዚህ መጽሐፍ የምታዩት ዝርዝር ነው።

ወያኔዎች ለ26 ዓመታት ኢትዮጵያን ከመቆጣጠራቸው በፊት በሥጋ ዘመድ አዝማድነትና በጋብቻ በቤተሰብነት እዛው በዛው መተሳሰራቸው ለሚቆጣጠሯት ኢትዮጵያ ቀላል እንደሚሆንላቸው በማሰብ የድሮ የትግራይ መሣፍንትና ነገሥታትን ቅጂ በመከተል ነበር የመጡት። ዘጠኝ የፖሊት ቢሮ አባሎች እና ወደ 30 የሚጠጉ ማዕከላዊ አባላት አብዛኛዎቹ በትዳር እና በዘመድ አዝማድ የተቆላለፉ ናቸው። ሌሎቹ በወያኔ ጥላ የተሰባሰቡ የብአዴን እና የመሳሰሉ አሽከሮቻቸውም ልክ እንደ ወያኔዎች እርስ በርስ በጋብቻ ተጠላልፈው የመጡ ናቸው። አስተዳደሩን የከፋ ካደረገው አንዱ የሥርዓቱ መሪዎች እና አስፈጻሚ አሽከሮቻቸው በዘመድና በጋብቻ ሐረግ ተቆላፈው ስለሠሩ እነ መለስ ዜናዊ ይዘውት የመጡትን ጸረ ኢትዮጵያ ፖሊሲ ለማስፈጸም እጅግ የቀለለ ነበር።

ኢትዮጵያ  ከዓለም ሙሉ የተለየ መሪ ታይቶባታል። የአገሪቱ መሪ ሆኖ የአገሪቱን ዳር-ድምበር፤ ክብር፤ ታሪክና ሰንደቃላማ በዓለም መድረክ ፊት ቆሞ የሚያንቋሽሽና የሚቃወም፤ አገሪቱን ለማፍረስ በሕግ የተደነገጉ 44 የጎሳ ባንዴራዎች አዘጋጅቶ፤ ለሚገነጠሉ ጎሳዎች አንቀጽ አዘጋጅቶ አገር ለማፍረስና ያገሪቷን ጥንታዊ የባሕር በሮቿን ለጠላት በማስረከብ የሚኩራራ ርዕሰ ብሔር የታየው በኢትዮጵያ ብቻ ነው። በዚህ ግለሰብ መመሪያ የሚመሩ ባለጊዜዎቹ ‘እኛ  መንግሥት ነን፤ መንግሥት ማለት ሕዝብ ማለት ነው ይሉናል። ፈላስፋው ፍሬዴሪክ ኒቺ “መንግሥት የክፉዎቹ ሁሉ ክፉ አውሬ ነው።” ይለናል።  መንግሥት በሁሉም ቋንቋዎች የሚዋሽ አፍ ነው። መንግሥት የተፈጠረው ለኒህ እልፍ አእላፍ ሰዎች ነው። እንዴት እንዴት እንደሚያባብላቸው ብቻ ተመልከቱልኝ። ሲያላምጣቸው፤መልሶ’መላልሶ’ሲያኝካው አያችሁልኝ?“ ይላል ‘ኒቺ’። አዎን በአውሬዎች መሃል ተከብበን እያላመጡ መልሰው መላልሰው አኝከውናል። “ኒቺ” በታምራታዊ ትንቢቱ “መንግሥት ሲሞት ቀስተደማና ይወለዳል” ይላል። ኢትዮጵያም በቀስተዳመና መቀነትዋ ዙርያ ብቅ ብላ እንደጥንቱ ሰንደቃላማዋን ይዛ የዚህ ስርዓት ሞት ታበስራለች። አንድ ቀን!

ወገኖች ሆይ! እስከዚያው ግን ዜግነታችንን በዘመናዮቹ በትግሬዎች መንግሥት በወያኔ ተነጥቀናል። በትዕቢት የተወጠሩ አብሮ አደጎቼ <<ትግሬዎች ወዳሉበት አትዝመት፤ ትግሬዎች ሳትይዝ አትዝመት>> የሚለውን የሰማይ ጣራ ለማፍረስ በሚንጠራራው ትዕቢታቸው እየተመሩ ሲራመዱ መሬቲቱ አፍ አውጥታ እስክትጮህ ይደበድቧታል። አገር ቤት ደርሶ ሲመጣ የታዘበውን የአንድ ወዳጄ ወዳጅ የላከለትን፤ የዘመኖኞቹ ጥጋብ እንዲህ ይገልጸዋል፡

“…እግዚአብሔር ይስጥልኝ ወንድሜ። ወደ ኢትዮጵያ ሄጄ ነበር የተወሰነ ወር ቆይቼ ነው የመጣሁት። የሰውን ፊት አይተው ይለያሉ ሊቃወመን ይችላል ብለው የሚያስቡትን ኤርፓርት ኢሚግሬሽን ቡት/ኪዮስክ/ ውስጥ ከሚቀመጡት ዘረኛ ትግሬዎች ጀምሮ። በተለይ ቦሌ መድሐኒአለም ፊት ለፊት በኤድና ሞል ዝቅ ብሎ ብዙ ዘመናዊ ባለ 5 ኮከብ ሆቴሎች ተከፍተዋል ሁሉም የትግሬ ናቸው። ነጮቹ “ሆቴል ዲስትሪክት” ይሉታል። የኛ ህዝብ “መቀሌ” እና “አፓርታይድ” ይለዋል ሰፈሩን። በተለይ ቬኒሺያን የሚባለው የትግሬ ሆቴል ገብተን 10 ዲቂቃ እንደተቀመጥን ካውንተሩ ላይ የሚቀመጠው እጅግ በጣም የጠገበ ሲራመድ መሬት የሚነቀንቅ ትግሬ የተቀመጥንበት ድረስ መጥቶ ያፈጣል። አስተያየቱ ሀሉ በጣም ነው የሚከብድው። ህዝቡ ኪሱ ውስጥ ያለውን ብር ቶሎ አራግፎ እንዲወጣ ነው የሚፈልጉት። ጥላቻቸው በግልፅ የሚታይ ነው። በዘረኝነት እና በጥላቻ ከተመረዘ ህዝብ ጋር መኖር በጣም ነው የሚከብደው። ህዝባችን በገዛ አገሩ ላይ እንዲሸማቀቅ እየተደረገ ነው። ባካባቢው ባሉት ሌሎች የትግሬ ሆቴሎች ውስጥም ተመሳሳይ ዘረኝነት ነው ያየሁት።” ይላል። “ይህ እጅግ በጣም የጠገበ ሲራመድ መሬት የሚነቀንቅ ትግሬ የተቀመጥንበት ድረስ መጥቶ ያፈጣል” ብሎ የነገረን በወጣትነት ዕድሜ ያለ የሆቴል ደምብ-ልብስ የለበሰ ዕብድ የሚያክል ሽጉጥ በእጁ ይዞ ደጅ ወጥቶ መኪና ላይ ተደግፎ ምድሩም ነፋሱንም ሲያስፈራራ በቪዲዮ የተቀዳ ልኮልኝ አይቼው፤ የትግራይ ሕዝብ እንዲህ ያለ የልጆቹ ዕብደት ተሎ ካላስቆሞው ዛሬ ‘ ነገ ’ ሲሆን አስቸጋሪ ፈተና ላይ ይወድቃል።  ሲበዛ ጥጋብ ሰንጥቋቸዋል። በገዛ አገራችን መቆሚያ መቀመጫ አሳጥተውናል። አገሪቷ ጠመንጃ ለያዙ ከትግሬ የመጡ ወሮበላዎችና ለልጆቻቸው እንጂ ለኛ ለዜጎች መኖሪያ እንድትሆን አልተፈቀደም። ይህን ቡድን በግልጽ መውቀስ ወይንም ተከታዮቹን መተቸት ለችግር ይዳርጋል። ጸሎታችን  ተቀይሯል። “ጌታ ሆይ ከጀርመን Gestapo (ጌስታፖ)፤ ከኢጣሊያው squadrist ፤ ከወያኔው ‘አጋአዚ’ ማረን” ማለት የዕለት ተለት የኢትዮጵያዊያን ጸሎት ሆኗል። ከጫካ የመጣ ዐውሬያዊ ተፈጥሯቸው ትችት አያውቅም፤ በድርጅታቸው እና በመሪዎቻቸው የሚነጣጠረውን ሂስና ትችት በፖለቲካ ዓይን አይመለከቱትም። ወያኔ ትግሬዎች ለምን ተተቸን በሚል ክፉ ቂም ያሳድራሉ። ቂማቸው እስከዕለተ ሞታቸው ለረዢም ጊዜ አብሮአቸው ይጓዛል። በዚህ መጽሐፍ የምታነቡት የቂማቸው መጠን ምን ያህል ርቀት እንደተጓዘ ወይም ሊጓዝ እንደሚችል የሚጠቁም ነው።

አገር ለነሱ ብቻ የተሰጠች ግዑዝ ዕቃ ነች። ሊቆርሷት፣ ወደብ አልባ ሊያደርጓት፣ ሊሸጧት፤ ሊለውጧት፤ ብጥስጥስዋን ሊያወጧት፤ በስጦታ ሊያበረክቷት ባለ ሙሉ ሥልጣን ናቸው። ቻይናዎች ሰው ሲገድሉ ለዲፕሎማሲ ግንኙነት ሲሉ ገዳዩን በሕግ ላለመጠየቅ በነፃ ይለቋቸዋል። የቻይና “ኢንቨስተሮች’ ‘የራሳቸው እስር ቤት’ መሥርተው ዜጎችን መደብደብና ማሰር፣ ደሞዝ ያለመክፈል መብት አላቸው  “በኢትዮጵያ ምድር!!”። የምድሪቱ ሉዓላዊ የጠረፍና የምድር አካላትዋ በውጭ ኃይላት በ “ድሮን” (በሰው አልባ አውሮፕላን) ተደፍራ እንድትሰለል ፈቃድ የመስጠት መብታቸው ጥያቄ ውስጥ አይገባም። ምንነታቸው የማይታወቁ ዓረቦችና የውጭ አገር ፈረንጆች በአገሪቷ የቆዳ ስፋት ውስጥ ተዘርግተው ያለምንም ቁጥጥርና ስጋት አንደ አሸን ተበራክተው የአገሪቷ ሉዓላዊ ገላ ይፈትሻሉ። በውስጧ የሚንቀሳቀሱ ፍጡራን ሉዓላዊ ክብራቸው በባዕድ ይረገጥ አይረገጥ ለትግሬዎቹ መንግሥታዊ መሳፍንቶች የተፈጠሩ ንብረቶች ናቸውና ዜጎች ምንም ዓይነት መብት የላቸውም። በሺዎች ሕይወት መስዋዕት  የተገኘ የጦር ሜዳ ድል እና ድምበር መልሰው ለታሪካዊ ጠላት የማስረከብ መብታቸው የተረጋገጠ ነው፡፡ ያን ሲያደርጉ አይከሰሱም፤ ማን ያበደ አለ የሚጠይቃቸው? ተጠያቂዎችም  ከሳሾችም፤ ፈራጆችም እነሱ ናቸውና ያለመጠየቅ የማይገሰስ መብት አላቸው።

ኢትዮጵያ በትግሬዎች ብቻ እንደተገነባች  አድራጊ ፈጣሪ አድርገው እራሳቸው ራሳቸውን ሰማይ በመስቀል ስለሚክቡ ዜጎች በነሱ ፈቃድ ብቻ ይንቀሳቀሳሉ፤ ሲፈልጉ ያድኗቸዋል፤ ሲፈልጉ  ይገድሏቸዋል፤ ሲፈልጉ ያሰድዷቸዋል፤ ሲፈልጉ-ያባርሯቸዋል፤ይዘርፏቸዋል፤ ይደበድቧቸዋል።
ወዳጄ ነፃነት በላከልኝ ባንድ ጹሑፉ ወያኔዎችን “ክፉ ዕብዶች’ ይላቸዋል። 4የታወቁ የዕብደት ዓይነቶች አሉ ይላል። Badmad, Mad-mad, Sad-mad, and Glad-mad. የሚባሉ። እነዚህ ሁሉ የዕብደት ዓይነቶች ወያኔ የተያዘበትን የአእምሮ ደዌ ለማወቅ ሞክሬ በመጠኑ የተጠጋጋልኝ የመጀመሪያው የዕብደት ዓይነት ነው – “ክፉ ዕብድ” ወይም “መጥፎ ዕብድ” የሚለው  ይላል። መጥፎ ዕብድ እየሣቀ መጥቶ በደቦል ድንጋይ ደረትህን ወይም ማጅራትህን መትቶ ሲጥ ያደርግህና በሞትህ እየሳቀና እየተዝናና በመጣበት መንገድ ሊመለስ ይችላል፡፡ ይህ ዓይነቱ ዕብድ ቀድሞውን የተለከፈበት የአእምሮ ህመም ከግድያና ስቃይ ጋር የተያያዘ በመሆኑ የሚያስደስተው ነገር ግድያና ስቃይ ነው፡፡ ለዚህ ዕብድ ሰዎችን ማሰቃየት ብቸኛው የደስታ ምንጩ ነው’እንደ ህወሓት!:“ዕብድና ዘበናይ የልቡን ይናገራል” ይባላል። አንድ ሰው ካላበደ መቼም በአንድ ጊዜ ጨለማና ብርሃን ለመሆን አይሞክርም፡- ዕብዱ ወያኔ አንዴ “የፍቅር ዓመት ይሁንልን” ይልና በዚያው አንደበት ስለፍቅር ብቻ የሚያዜመውን ብላቴና የሙዚቃ ምረቃውን መከልከሉ አላንስ ብሎ ልጁን በአሸባሪነት መፈረጁና በጦር ለመውጋት ሲዘጋጅ ማየቱ ስም የማይገኝለት ዕብደት ነው፡፡ በአንዲት ትልቅ ሀገር ውስጥ አንድ ግዙፍ መንግሥት ከአንድ ተራ ዜጋ ጋር የእልህ ግብግብ ውስጥ ገብቶ ሲዳክር ማየት ዓለምን ሳያስገርምና የመጀመሪያው ትንግርት ሳይሆን አይቀርም፡፡ ቴዎድሮስ ካሣሁን ከጊታርና ከማሲንቆ ያለፈ መሣሪያ ሳይኖረው ወያኔን በፍቅር ስብከቱ ብቻ እንዲያ ሲያንበጨብጨው መታዘብ አስደማሚ ከመሆን አልፎ የወያኔን ሰብኣዊ ተፈጥሮ እንድንጠራጠር የሚያደርግ ልዩ ክስተት ነው፡፡ ወያኔ እንደሚመስለኝ ከጦር መሣሪያና ከባዶ ጉራና ፉከራ  ይልቅ ይህን  መሰሉን እንደሐምሌ ዝናብ እየሰረሰረ የሚገባን የፍቅር መዓዛ በጣም ይፈራል፡፡ ፍቅር የሚያርደውና የሚያሸብረው ደግሞ ሰይጣንንና የሰይጣን የሆነን ብቻ ነው፡፡ እናም ወያኔ ባጭር ቃል ሰይጣን ነው፡፡ ይላል ወዳጄ ነፃነት። በነዚህ ጤና በራቃቸው በቀወሱ ጎስታፖዎች   ዜጎች ያለማቋረጥ ፤ ይጠለፋሉ፤ ይዘለፋሉ፤ ይሰወራሉ፤ ዜጎችን ያለ ነገዳቸው የግዴታ ነገድ ይሰጧቸዋል ። ከ500 በላይ ሶዶማውያን ጌይ/ ለዝቢያን) በሽርሙጥና ተዳዳሪነት ተደራጅተው የርዕሰ ከተማዋ ጎዳናዎች “በሃይ ሂል” የግብረሰዶማዊ  ጫማዎች  ይረገጣሉ። የኢሉሙናቲ ሃይማኖት አስገብተው የገበሬው ቤተሰብ  እንዲበክሉ አደርገዋል (በመጽሐፉ ውስጥ የተካተቱ ፎቶግራፎችን ይመልከቱ)። የአህያ ሉካንዳ መርቀው ከፍተዋል። “በሬ ከበላህ የአህያ ሥጋ ምን ከፋህ?” እያሉ በሬ እና አህያን እያነጻጸሩ አህያ መብላት ነውር እንዳልሆነ ሳያፍሩ ይሰብኩናል። አገሪቱ  በሃይማኖት ሕግ አትተዳደርምና ከአህያ ሥጋ ጋር ተለማመዱ ብለውናል። “ቆሻሻ የሚበላ ሕዝብ ይዘን አህያ ለምን ስትሉ አታፍሩም? እሱን በልታችሁ ከረሃብ በወጣችሁ በማን ዕድላችሁ!” ይሉናል ባለጌዜዎቹ። እግዚኦ መሃረነ ክርስቶስ!!

ጉራቸውና ድንፋታቸው መጠን ስለሌለው፤ እነሱ አምበሳ ሌለው ጥንቸል አድርገው በመሳል፤ “እንኳን ሰው፤ ግዑዝ ያስገረመ” በሚል አስካሪ ሙዚቃ እየጨፈሩ ከሰውነት ደረጃ ወጥተው ከመንጋዎቻቸው ጋር በሚበሉበት አፋቸው ግፍ እየተናገሩበት አብረው በማይጨበጥ ዓለም ውስጥ ገብተው አስደንጋጭ ደወል ይደውላሉ።

እንኳን ከዜጋ ከጠላት አንደበት ይወጣሉ ተብለው በማይታሰቡ አስደንጋጭ ዘለፋዎች አገርን፤ ሰንደቃላማንና ሕዝብን በተናዳፊ ምላሳቸው ሲዘልፉ ለነገ አይሉም። ታሪክን አይፈሩም። አረጋዊያንን በአለንጋ ይገርፋሉ፤ በልጆቻቸው ሬሣ ጎን ተቀምጠው የሚያለቅሱ እናቶችን በዱላ ይደባደባሉ፡፡ የአሸናፊነትና የጊዜ  ትርጉም አያውቁም። በሚውረገረገው የዕብደት መስተዋት በCollective Narcissism ታውረዋልና ጊዜ እንደሚጥል  አይረዱም። ጸሐፊው ዳግማዊ ጉዱ ‘አሸናፊነትን ከማያወቅ አሸናፊ ይሰውረን!” ይላሉ፤ እውነትም ይሰውረን!

የሚያረጉት ሲያጡ፤ ትንሿ ትግራይን  በ‘ሲም-ካርድ’ (Sim Card ) ሰይመው፤ ትልቋ ኢትዮጵያ ‘ግዑዝ’ የቴሌፎን ቀፎ ብለዋታል። ያለ ትንሺትዋ ትግራይ ትልቋ ኢትዮጵያ ሕይወት ሊኖራት አይችልም የሚለው ትዕቢታቸው አብጦ ፈንድቷል። ትግራይ የኢትዮጵያ ‘ሲም ካርድ’ ነች። “እኛ ትግሬዎች ኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳንሆን፤ ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ ያደረግንና የመሠረትን ነን። ምስክር የምንሆንለት ካልሆነ በቀር የእኛ ኢትዮጵያዊነት ምስክር አያስፈልገንም፤ ብታምኑም ባያምኑም፤ ሃቁ ያ ነው” ይሉናል በልዕለነት የሚመኩ የትግራይ ፋሺስት ምሁራን። ሰዎቹ ከምድሪቱ እትብት ተለይተው ብቻቸውን ርቀው የሚጓዙ አስፈሪ ፍጡራን ሆነዋል።በቅኝ ግዛት ያልተገዛው ይህ ኩሩ ሕዝብ የሚቀጠቅጡት የወታደሮቹ ማዕረግ ስም፣ ንግድ ቤቶቹ፣ ትምህርት ተቋማቱ፣ከ/ሀገሮቹ(ዞን/ስቴት….፤) አብዛኛዎቹ ጎዳናዎቹ በባዕድ ቋንቋ ተሰይመዋል። የወታደሮቻቸው ማዕረግ ኮማንደር፣ ኮንስታብል፣ ኢንስፔክተር፣ ሱፐር ኢንስፔክተር፣ ሱፐር ኢንቴንዳንት… ነው። ለምን? ብለን በአግራሞት ስንጠይቅ የሚመልሱልን መልስ ‘ሻምበል፣ ሻለቃ፣ መቶ አለቃ፣ ሃምሳ አለቃ፣ አሥር አለቃ…. የሚሉ አገር በቀል ወታደራዊ መጠሪያዎች የአማራዎች ነውና ከኬኒያ ከናይጀሪያ ወስደን ሰይመናቸዋል ይሉናል። አማራና አማርኛን ለማጥፋት የተነሳንበት ዓላማ ነውና ስትፈልጉ አልቅሱ ይሉናል። አስገራሚ የሚያደርገው ደግሞ የማናጋቱን ሂደት ለማከናወን “በሕግ የተፈቀደ” የጥላቻ ቅስቀሳ በኢትዮጵያ ላይ፣ በክርስትያን ማኅበረሰብ ላይ፣ በአማራ ኅብረተሰብ ላይ እንዲጻፍና እንዲነገር በሕግ ተፈቅዷል። የጥላቻ ሃውልቶች ተመርቀው ተተክለው ይታያሉ። ባለጊዜዎቹ በይፋ በቴሌቪዥን፣ በራዲዮ፣ በጋዜጦች ወዘተ. ይህንኑ የጥላቻ ንግግር በመናገር ኅብረተሰቡ እንዲሸማቀቅ እና ውርደቱ ሕጋዊ እንዲሆን አድርገዋል። አብዛኛው ዜጋ አጥቂዎቹ በሚሰጡት የመጠላለፊያ ፖለቲካ  ወጥመድ ውስጥ ገብቶ፣ እርስ በርሱ በጠላትነት እየተፈራራጀ፣ የየራሱን ባንዴራ እያሠራ በማውለብለብ “ኢትዮጵያን” ማዕከላዊ የጋራ ጠላት በማድረግ የተሰጠውን የማናጋት ሤራ የየራሱን መጥረቢያ ይዞ በመገዝገዝ ላይ ነው። በፋሺስቶቹ የተሰጣቸው “የኤትኒክ ፌደራሊዝም አስተዳዳር” አገርን የማናጋት ሤራ ለማከናወን “ጎሣዎች” የተነገራቸው የጋራ ጠላት ተብለው የተሰየሙ ‘ተዋህዶ ሃይማኖትን፣ አማርኛንና አማራን’ በመጻረር ጎሣዎች አጥቂዎች የጠነሰሱላቸው መርዝ በጥብጠው እየጠጡ ሀገርን በማናጋቱ ሂደት ተዋናይ ሆነው የየራሳቸውብ ምሣር ይዘው አገሪቱን በመገዝገዝ ተጠምደው ራሳቸውን በማጥፋቱ ሂደት ላይ ይገኛሉ። የፖለቲካ፣ የሚዲያ፣የሃይማኖት፣የጎሣ ወዘተ.. ወዘተ…. ተቋማት “ያገሪቱን ግንድ” በመገዝገዙ፣ በማናጋቱ ትዕይንት ውስጥ እጃቸውን በማስገባት በሳብቨርሲቡ/ በጥቃቱ ዘመቻ አቀነባባሪ በወያኔ  እየተመሩ ወደ አስፈሪው ሂደት እየወሰዱን ነው። የሃይማኖት ተዋናዮችን ስትመለከቱ በተዘረጉላቸው “ideological/subversion (የእምነት ብከላ) ወጥመዶች ገብተው ከዓረቦች በአላህ ስም በዋሃቢም ስም፣ ከምዕራቡ ዓለም ደግሞ በጴንጤና አይሁድ ስም  እየተጠመደ በማያውቀው መርዝ እየተመረዘ “በማናጋቱ ሂደት” ውስጥ እየተጓዘ  ነው ማለት ነው። የኦሮሞ ፋሺሰቶች አማራን <አማርቲቲን ነማ ሚቲ> “አማራ ከሰው በታች ነው” የሚለውን ዘፈን እየዘፈኑ ቁጥራቸውን ለማወቅ በሚያስቸግር አማራዎች ከነ ነብሳቸው ወደ ገደል እየተጨመሩ፣ ሴቶች ከጡታቸው የተቆረጠ ሥጋቸውን እንዲጎርሱ እየተደረገ አሰቃቂ ግድያ ሲፈጸም፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አማራዎች ከምድር ሰውረናል ብለው ሲኩራሩ፣ ዓለም ምን አለ እንጂ እኛስ ምን አልን!? የሚል ጠያቂ አልተገኝም። ይህም ሆኖ ‘የመቻቻል ፖለቲካ” በተቃዋሚዎች እየተሰበከ የዘመኑ ማደንዘዣ ዕፅ ሆኖ ሙታን እንዳይዘከሩ ለገዳዮች ምቹ ሽፋን ሆኖላቸዋል። አንድ የአንድነት ፓርቲ አመራር አባል “መለስ ዜናዊ ሞቷልና የሞተን ሰው ስም እያነሳን ሙትን መውቀስ  እናቁም” ብለው በሚሰብኩን የፖለቲካ ቀሳውስት እየተሰበክን አረሙን መረማመድ አልቻልንም።

የደናቁርት አክሊል የደፉ የባለጊዜዎቹ ጥጋባቸው ሞልቶ መቋጠሪያ አጥቷልና የባህል ቅኝ ተገዥ አድርገውናል። ስማችን፣ ዜግነታችን፣ አርማችን፣ መታወቂያችንንና እኛነታችንን የመቀየር ሥልጣናቸው የማይገሰስ ‘ምሉዕ’ ነው። እነሱ ወደ ፈጣሪነት እኛ ወደነሱ ፍጡርነት ተቀይረናል። በዛች አገር ውበትና ነፃነት የቀኑ፤ ክፋት የተጠናወታቸው የሩቅና  የቅርብ ጠላቶች ባጠመዱላት ወጥመድ፤ ጤና ባጡት ዕብድ ልጆቿ ተባባሪነት በለኮሱት ሴራና ጦርነት ውብና ክቡር ገላዋ እርቃንዋ ወጥታ ለጠላቶቿ ተገልጣ በሐፍረት ተኮማትራ ትታያለች።  ወላጆች ችግር ውሰጥ ገብተዋል። አባት ልጁን ወደ ዓረብ አገር ወደ ሽርሙጥና ልኮ በሚላከለት ‘የሆር ሞንገር” ገንዘብ እህል ሸምቶ ቆርሶ እንጀራ ሲበላ “የእርም ገንዘብ” አልበላ ብሎት ከጉሮሮው ጋር ውረድ አልወርድም ትግል ገጥሞ እምባ ይተናነቀዋል። አንዳንዱም እራሱን ገድሏል። ባለጊዜዎቹ ብዙውን ዜጋ ቁጭት ውስጥ ከትተውታል። ቁጭታችን በታረክ ማኅደር እንድናስመዘግብ ይኼው ተገድደናል። የሕይወት አሳዛኙ ክስተት ሞት ሳይሆን ሳንሞት የቀበርነው ቁጭት ነው። እንደ ትግሬነቴ የትግራይ ፋሺስቶችን ተፋልሜአቸዋለሁ በአገሬ ሞት ያደረብኝ ቁጭት ከመሞቴ በፊት ቀድሞኝ እንዲቀበር አልፈቀድኩም። ስለሆነም እነሆ ቁጭቴ ከናንተው ጋር ቆሞ ይነጋገራል።  ………….
መልካም ንባብ !
መጽሐፉን ለማግኘት $30.00 የፖስታ አገልግሎት ደራሲው ይሸፍነዋል።
getachre@aol.com (408) 561-4836
ጌታቸው ረዳ
p.o box 2219 San Jose, CA 95109