Skip to content

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ የእስር ጊዜውን ቢያጠናቅቅም ባላወቅነው ምክንያት የዝዋይ ማረሚያ ቤት አስተዳደር አልፈታውም ብሏል ሲል የተመስገን ወንድም ለቢቢሲ ተናግሯል።
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የ3 ዓመት የፍርድ ጊዜውን ዓርብ (ጥቅምት 3) ቢያጠናቅቅም የዝዋይ ማረሚያ ቤት አስተዳደር ግን ያለምንም ምክንያት ተመስገንን ለመልቀቅ ፍቃደኛ ስላልሆነ ወደ መጣንበት አዲስ አባባ እየተመለስን ነው ሲል ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ በስልክ ገልጾልናል።
”ትናንት ሃሙስ የእስረኞች አስተዳደር ክፍል ውስጥ ያገኘሁት ግለሰብ ተመስገን የሚፈታበትን ቀን ጠይቄው መዝገብ አገላብጦ ዛሬ እንደሚፈታ አረጋግጦልኝ ነበር። የእስር ጊዜውም ስለሚጠናቀቅ እንደሚፈታም እርግጠኛ ነበርኩ” ይላል ታሪኩ።
ተመስገን፤ ታሪኩ እና ጓደኞቹን በማረሚያ ቤት ውስጥ ሊያናግራቸው ሲመጣ ባልተለመደ መልኩ በስምንት ወታደሮች ታጅቦ እንደነበር ወንድሙ ይናገራል።
በነበራቸውም ቆይታ ”መፈታት ነበረብኝ ነገር ግን እንደማይፈቱኝ ነግረውኛል፤ ለምን እንደሆነ አላውቅም” ሲል ተመስገን ነግሯቸዋል።
የተመስገን እናት፣ የቤተሰብ አባላት እና ጓደኞቹ የእርሱን መፈታት ተስፋ አድርገው በጉጉት እየጠበቁ ነበር።
ይፈታል በሚል ተስፋ በዝዋይ ማረሚያ ቤት ውስጥ እና ከዚህ ቀደም የፃፋቸውን የተለያዩ ፅሑፎች ስብስብ ”ጊዜ ለኩሉ” በሚል ርዕስ በመፅሃፍ ታትሞ ገበያ ላይ ውሏል።
Like this:
Like Loading...