
የክብር ንጉስ ይገባ ዘንድ በሩ ይከፈት፤ የክብሩ ንጉስ በቂምና በጥላቻ መካከል ወደ ውስጥ አይዘልቅምና የምዕመኑ ፀሎት እና ምልጃም ከቅዱሳን መላዕክቱ ፅና ከእጣኑ ጢስ ጋር በእግዚአብሔር ፊት እንዲያርግ፤ በዚህ አጋጣሚ የተጣሰው ቀኖና ቤተክርስቲያን ይታረም። በብፁዓን አባቶች መካከል እርቀ ሰላም ይውረድ። ሁለት ሲኖዶስ መንበር አይፀናምና እርቀሰላም በማውረድ በቤተክርስቲያን ሰላም ይውረድ። ቀዳዳ እየፈለገ ወደ ውስጥ ለመዝለቅ የሚያደባው የተሐድሶ ተኩላም በሩ ይዘጋበት። በአቡነ ጳውሎስ ዘመን ከዳር ደርሶ ሳለ በህወሓት መንግስት እንቢተኛነት የተደናቀፈው እርቀ ሰላም ይፈፀም።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ እና ብፁዕ አቡነ ማትያስ ስለ ቤተክርስቲያን አንድነትና ሰላም በእናንተ ዘንድ (በውጭ እና በሀገር ውስጥ ባለው ሲኖዶስ) መካከል እርቅ ይሁን። ይህ ሳይሆን ቢቀር ያለ ይቅርባይነት የሚያርግ መስዋዕት የሚሰማ ፀሎት እንደሌለ አስተምራችሁናልና ሁሉ ከንቱ ነው። ልጆቻችሁ ስለ እርቅ እንማፀናለን።
በትህትና !
በትህትና !