የሆማ ቤይ ካውንቲ የፓርላማ ተወካይ ከኬንያ 47 ካውንቲዎች 40ዎቹ ተገንጥለው ‹ሕዝባዊት ዲሞክራሲያዊት ኬንያ› የምትባል ሌላ ሐገር መመስረት እንደሚፈልጉ የሚጠይቅ ረቂቅ አዋጅ ለምርጫ ቦርዱ አቀረበ። ይህ ረቂቅ አዋጅ በኬንያ ሕገ መንግስት አንቀፅ 256(መ) መሰረት የተረቀቀ መሆኑን የምርጫ ቦርድ በትላንትናው እለት በማረጋገጡ ፓርላማው ውስጥ ወደሚገኙት ሁለት ምክር ቤቶች እንዲያቀርብ ይሁንታውን ሰጥቶበታል።
***

እንደ ፒተር ካሉማ የሆማ ቤይ የፓርላማ ተመራጭ አነጋገር በተለይ በባለፈው የጥቅምት 26 ምርጫ ላይ ያልተሳተፉ አራት ግዛቶች ባልመረጡት ፕሬዝዳንት መተዳደር አይፈልጉም። ይህን አባባሉን የሚያረጋግጠውም ደግሞ እስካሁኗ ቅፅበት ድረስ የ7 ካውንቲ ምክር ቤቶች ኡሁሩ ኬንያታን እንደ ፕሬዝዳንትነት እንደማይቀበሉ ወስነዋል። በሌሎችም ካውንቲዎች በኡሁሩ ኬንያታ ፕሬዝዳንትነት ዙርያ የመተማመኛ ድምፅ ውሳኔ የመስጠት ስብሰባ በቀጣይ ቀናት እንደሚካሄድ ለማወቅ ተችሏል። በመሆኑም በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 256(መ) መሰረት የኬንያ ሕዝብ ባልመረጠው ፕሬዝዳንት የመተዳደር ግዴታ ስለሌለው፤ ፕሬዝዳንቱ የመረጣቸውን ክልሎች መምራት እንደሚችልና ፕሬዝዳንቱን ያልመረጡት (ድምፅ ያልሰጡት) ክልሎች የራሳቸውን ሐገር መስርተው የራሳቸውን ፕሬዝዳንት መምረጥ እንደሚፈልጉ ተናግሯል።
***
መንገዱ ምን ይመስላል?
***
ፒተር ካሉማ ያቀረበው ረቂቅ አዋጅ ከፍፃሜ ለምድረስ ሁለት ዓይነት መንገድ ይኖረዋል። የመጀመርያው ረቂቅ አዋጁን ፓርላማው ውስጥ ላሉ ሁለት ምክር ቤቶች አቅርቦ ባንዱ ምክር ቤት ብቻ 2/3ኛ ድምፅ ማግኘት አለበት። ከዚያ በኋላ የፕሬዝዳንቱን ይሁንታ ተከትሎ ለመላው የፓርላማ ተወካዮች ውይይት ይቀርባል። ውይይቱን ካለፈ ከ30 ቀናት በኋላ ዓዋጅ ይሆንና የኬንያ ሕዝብ በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 255(2) መሰረት በ90 ቀናት ውስጥ ሕዝበ ውሳኔ ለማድረግ ይገደዳል ማለት ነው።
***
ፒተር ካሉማን ከዚህ ሁሉ ውጣ ውረድ የሚያድነው ሁለተኛ አማራጭም ከፊቱ ይገኛል። ሁለተኛው አማራጭ የ1 ሚልዮን መራጮችን ፊርማ ማሰባሰብ ያካትታል። ከዚያም እነዚህ ፊርማዎች ትክክለኛ ስለመሆናቸው በምርጫ ቦርድ ከተረጋገጡ በኋላ ይህ ረቂቅ ለ47ቱም ካውንቲ ምክር ቤቶች እንዲወያዩበት ይተላለፍላቸዋል። ምክር ቤቶቹ በ90 ቀናት ውስጥ ተወያይተውበት ውሳኔ ማሳለፍ ይጠበቅባቸዋል። ከ90 ቀናት በኋላ አብዛኛው ምክር ቤት ካፀደቀው ለፕሬዝዳንቱ ይቀርብለትና የኬንያ ሕዝብ በ90 ቀናት ውስጥ ሕዝበ ውሳኔ ያካሂዳል ማለት ነው።
***
ረቂቁ ከዚህ ሁሉ ሂደት በኋላ ዓዋጅ የመሆን እድል ባይኖረው እንኳን የኬንያ ሕዝብ በቀጥታ በረቂቁ አዋጅ ይሁን ወይንም አይሁን ላይ ድምፅ እንዲሰጥበት ሊደረግ ይችላል።
***
እንግዲህ ይህ ረቂቅ ከተሳካና በዓዋጅነት ፀድቆ ስራ ላይ ከዋለ ወደፊት ከታች በምስሉ ላይ የምታዩዋቸውን ሁለት ጎረቤት ሀገራት እናገኛለን ማለት ነው።
***
ይህ በእንዲህ እንዳለ … እንዲል ተመስገን በየነ… ኬንያውያን ኡሁሩ ኬንያታን ከስቴት ሐውስ ለማስወጣት የሚያደርጉት ዘርፈ ብዙ ትግል በጠቅላይ ፍርድ ቤት ውስጥም ቀጥሏል። ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ትላንትና ጀምሮ በከሳሾችና(ተቃዋሚዎች) በመልስ ሰጪዎች (ምርጫ ቦርድና የጁቢሊ ጠበቆች) መሐከል ኃይለኛ ክርክሮችን እያስተናገደ ይገኛል። የፍርድ ቤቱ ሂደት በቀጥታ ስርጭት በሲቲዝን ቲቪ ዌብሳይት ላይ እየተላለፈ ስለሆነ ማየት ትችላላችሁ።
***
ተቃዋሚዎች ሐሙስ እለት ከአሜሪካ ለሚመለሰው መሪያቸው ራይላ ኦዲንጋ ታላቅ የሚባል አቀባበል እያዘጋጁ ቢሆንም ፖሊስ ደግሞ ለሰልፍና እንደዚህ ዓይነት ሥነ ሥርዓት ፈቃድ አልሰጥም ብሎ ፍጥጫ ላይ ናቸው። እንደሚታወቀው ሰልፎችና የዚህ ዓይነት ስነ ስርዓቶች ማሳወቅ እንጂ ማስፈቀድ ስለማይጠበቅባቸው ተቃዋሚዎች የፖሊስ ጄኔራሉን መግለጫ ከቁብም የጣፉት አይመስልም።
***
ምስል ቁ. 1 – ፒተር ካሉማ
ምስል ቁ.2 – ረቂቅ አዋጁ በካርታ ላይ ሲታይ…

 

MP Kaluma drafts secession Bill to form ‘People’s Republic of Kenya’

 

Homa Bay Town MP Peter Kaluma speaks to journalists outside Parliament. /JACK OWUOR
Homa Bay Town MP Peter Kaluma speaks to journalists outside Parliament. /JACK OWUOR 

Homa Bay Town MP Peter Kaluma has drafted a bill seeking to split the country into the People’s Republic of Kenya and the Central Republic of Kenya.

In the Bill to be tabled in Parliament, Kaluma wants 40 out of the 47 counties to secede and form the People’s Republic of Kenya.

Kaluma argues that these counties have continually been discriminated upon by successive governments.

The Bill says while all important public appointments have remained the eternal; preserve of a few, the national budget is permanently skewed to benefit a few groups, communities and regions while marginalising the rest.

The MP says the rest of the country has been rendered mere tax payers without corresponding rights to equal opportunities and service.

“The current administration has captured the state and totally emasculated Parliament, commissions and independent offices established to secure good governance,” the draft Bill reads.

According to the Bill, the People’s Republic of Kenya would include major counties such as Nairobi and Mombasa.

The People’s Republic would consolidate vote-rich areas such as the Rift Valley, Western Kenya and the Coast.

The seven counties that would form the Central Republic of Kenya are Nyeri, Murang’a, Kiambu, Kirinyaga, Nyandarua, Embu, and Tharaka Nithi.

“The objective of the Bill is therefore to amend the constitution to split to allow for the creation of a new state to give effect to the aspirations of the people of Kenya,” Kaluma’s Bill reads.

He has accused President Uhuru Kenyatta’s administration of being ready to do anything including “political assassinations, manipulations of ethnic census and voter register, flagrant rigging of elections, systematic suppression of other groups and communities to retain political and economic power”.

Kaluma argues the marginalised communities do not feel fully and equally Kenyan and are determined to halt the current state capture.

Governors Hassan Joho (Mombasa) and Amason Kingi (Kilifi) have been leading secession calls in the Coast region.

They have cited political and economic marginalisation in the call supported by a host of Opposition MPs from the region.

More on this: [VIDEO] Coast must secede to end marginalisation, Joho and Kingi say

If Kaluma’s Bill goes through Parliament, he will need two-thirds of the members in the National Assembly (233 of the 349) and the Senate (45 of the 67) to support it.

Currently, Jubilee has a majority in both Houses.

But should the Bill be passed in both Houses the Speakers would present it to the President who will ask IEBC to conduct a referendum in 90 days.

Alternatively, the MP can collect one million signatures, which are then certified and presented to the electoral agency.

Source   –  THE  STAR  (Kenya)