November 23, 2017 05:36

በይርጋ አበበ

የህወሓት ታጋይና በኋላም የአየር ኃይል አዛዥ የነበሩት ሜጀር ጄኔራል አበበ ተ/ሃይማኖት ከአየር ኃይል አዛዥነታቸውና ከህወሓት/ኢህአዴግ አባልነታቸው ራሳቸውን ካገለሉ በኋላ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አስተማሪ ሆነው ቆይተዋል። በኋላም በጡረታ ተገልለዋል። ኢህአዴግ ሥልጣን መልቀቅ የነበረበት በ1987  ዓ.ም ነበር። ሆኖም ሁልጊዜም እኔ አውቅልሃለሁ በሚለው አመሉ እሥካሁን ሥልጣን ላይ ቆይቷል ሲሉ ይናገራሉ። በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከሰንደቅ ጋዜጣ ጋር ሰፋ ያለ ቃለምልልስ አድርገዋል። ይህንንም ቃለምልልስ ለአንባቢያን በሚመች መልኩ አዘጋጅተን አቅርበነዋል።

ሰንደቅ፡

– ውይይታችንን በወቅታዊ ጉዳይ እንጀምር። አገራችን የምትገኝበት ፖለቲካዊ ሁኔታ እንዴት ያዩታል?

ጄኔራል አበበ ጠቅለል አድርገን ስናይ ሁለት ነገሮችን እናገኛለን። የመጀመሪያው ወቅታዊ ጉዳይ ነው። በሌላ በኩል ደግሞመሠረታዊ የሕገ-መንግሥት ጉዳይ አለ። ሕገ-መንግሥት በእኔ አመለካከት የኢትዮጵያን የሰላም፣ የዴሞክራሲ እና የልማት ጉዞ የቀየሰሕገ-መንግሥት ነው። ለኢትዮጵያም የሚበጃት አሁን ያለው ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ነው። ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱ ችግርየለበትም። ችግር ያለበት በፖለቲካው የመንግሥት ሥርዓቱ ነው። ይህ ችግር ደግሞ መሠረታዊ የዴሞክራሲ ችግር ነው። የዴሞክራሲችግር ባይኖርበት ኖሮ አሁን ያለው ፖለቲካዊ ቀውስ አይታይም ነበር።

በነገራችን ላይ የፖለቲካ ቀውስ የሌለበት አገር ያለ አይመስለኝም። በአውሮፓም ሆነ በአሜሪካ አለ። ልዩነቱ እነሱ ጋ ያለው የቀውሱደረጃ እና ቀውሱ የሚፈታበት መንገድ ነው። በእነሱ የችግር መፍቻ ተቋሞች አሉ። እኛ ጋ ግን እንደዚህ አይነት መሠረታዊ የሕዝብጥያቄዎች በሚነሱበት ጊዜ መልስ ሊሰጡ የሚችሉ ተቋሞች የሉንም።

ሰንደቅ፡

– ቀውስ መፍቻ ተቋማት የሚሏቸው የዴሞክራሲ ተቋሞች የሚባሉትን ነው፤ የሲቪክ ማኅበራትን?

ጄኔራል አበበ፡– ሲቪክ ማኅበራትም፣ ፓርቲዎችም፣ ሕግ አውጭውም፣ ሕግ አስፈፃሚውም ሆነ ሕግ ተርጓሚውም እነዚህ በሙሉእየሰሩ አይደሉም። ስለዚህ የሕዝቡን ፍላጎት ለመመለስ የሚያስችል ሁኔታ የለም። የሕዝብን ጥያቄ በሰላም መፍታት ስላልተቻለ ነውሕዝቡ ወደ ኃይል እየሄደ ያለው። በመሆኑም አሁን ያለው ፀረ-ዴሞክራሲ አያያዝ ካልተፈታ ወደ ትልቅ ችግር ነው የምናመራው። ነገርግን ይህን ወቅታዊ ቀውስ ወደተሻለ ደረጃ መቀየር የሚቻልበት ዕድል አለ ብዬ አስባለሁ።

ከዚህ በፊትም ኢትዮጵያ ውስጥ ቀውሶች ነበሩ። ነገር ግን አሁን ያለውን ቀውስ የፌዴራል ሲስተሙ የፈጠረው እንደሆነ ሲናገሩእሰማለሁ። በደርግ ጊዜ ያ ሁሉ ጦርነት ሲካሄድ የፌዴራል ሥርዓት ስለነበረ አይደለም፤ ያ ሁሉ ሕዝብ ያለቀው። አሁን ያለው ችግርየተፈጠረው በፌዴራል ሥርዓቱ ሲስተም ሳይሆን የግለሰብና የቡድን መብት ባለመከበሩ ነው።

ሰንደቅ፡– የፌዴራል ሥርዓቱ የአንድነታችን መሠረት ነው ተብሎ በተደጋጋሚ ቢነገርም፤ ቋንቋን መሠረት ያደረገው የአገሪቱ የፌዴራል ሥርዓት ግን በተለያዩ አጋጣሚዎች የሚነሱ ግጭቶችን የብሔር መልክ እያላበሳቸው ይገኛል። ለዚህ ደግሞ ችግሩ የፌዴራል ሥርዓቱ ሥረ-መሠረት ያደረገው ዘውግን በመሆኑ ነው ይባላል። እውን የቀደመው ሀሳብዎ ለዚህ መልስ አለው?

ጄኔራል አበበ፡– በእርግጥ የከፋ ጦርነት የነበረው በደርግ እና በኃይለሥላሴ ዘመን ነው። ጦርነቱ የተከናወነውም ብሔሮችናብሔረሰቦች ተደራጅተው የሚያካሂዱት ነበር። ለምሳሌ በትግራይ ህወሓት እንዲሁም በኦሮሚያ ኦነግ ያውም እስከመገንጠል የሚሄድጦርነት ነበር። አሁን የሚሆነውን ሥንመለከት ግን ዴሞክራሲ በመጥፋቱ የተፈጠረ መሆኑን ነው። ምክንያቱም ማስተንፈሻ የሚሆነውዴሞክራሲ በመጥፋቱ ሕዝቡ ወደ አላስፈላጊ መንገድ እንዲሄድ ያደርገዋል። ይህ “ዘርን” ማዕከል ያደረገ ጥቃት አድሃሪ ነው። በጣምመጥፎ ነው።

ግን ይህ ነገር እንዴት መጣ? የሚለው ጥያቄ ሲነሳ፤ ለምሳሌ በኦሮሚያ የነበረውን ግጭት ብናነሳ፤ ሕዝቡ ያነሳውን ጥያቄ የክልሉ ገዥፓርቲ ኦህዴድ በሰላማዊ መንገድ መፍታት አልቻለም። ስለዚህ በዚህ መሀል መንገዱ የተሳሳተ ይሆናል። ሰላማዊ በሚሆንበት ጊዜ እናጥያቄዎች በዴሞክራሲያዊ መንገድ በሚፈቱበት ጊዜ የትምክህት እና ጠባብነት አመለካከቶች ቦታ አይኖራቸውም። ነገር ግን ተቃራኒውበሚሆንበትና በነፃነት መነጋገር በማይችልበት ጊዜ ወደ አንድ ጫፍ ይሄዳል። ይህ ደግሞ በጣም መጥፎ ነው።

ጥያቄው ይህ ለምን ሆነ? ብለን ሥንጠይቅ ዴሞክራሲ እንዲኖር የሚጠይቀው ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት፤ ዴሞክራሲ ሳይኖር ሲቀርየሚፈጠር መሆኑን ነው። ምክንያቱም ዴሞክራሲ ከሌለ መንግሥታዊ ሥርዓቱ ፌዴራላዊ ይሁን ወይም ሌላ የከፋ ጦርነት እና ግጭትይፈጠራል። በደርግ ጊዜ የነበረውን ማየት ይቻላል። በደርግ ጊዜ ሕገ-መንግሥቱም ሆነ ፖለቲካው ፀረ-ዴሞክራሲያዊ ነበር። አሁን ግንሕገ-መንግሥቱ ዴሞክራሲያዊ ሲሆን፤ ፖለቲካው ደግሞ ፀረ-ዴሞክራሲያዊ ነው። ስለዚህ ህዝቡ ጥያቄ ያቀርባል። ይህ በሚሆንበትጊዜ ከሁሉም ፅንፍ ያለው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ውይይት መካሄድ ነበረበት። ግን ደግሞ ማካሄድ አልተቻለም እንጂ ቢካሄድ ኖሮመፍትሄ ይመጣል። ይህ በማይሆንበት ጊዜ ግን አጋጣሚውን ፅንፈኛው ኃይል ይጠቀምበትና የብሔር መልክ ያላብሱታል።

ሰንደቅ፡

– እርስዎ በሚሉት የፌዴራል ሥርዓቱ ችግር የለበትም ብለን እንስማማ። ሕገ-መንግሥቱንም ችግር የለበትም ብለን እንቀበል። ነገር ግን የፌዴራል ሥርዓቱንም ሆነ ችግር የለበትም የሚሉትን ሕገ-መንግሥት የመሠረተው የፖለቲካ ሥርዓት ዴሞክራሲን ሰጥቶ ለመቀበል ተፈጥሯዊ ባህሪ አለው?

ጄኔራል አበበ፡– ይህ የአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ (Context) ነው። እኛ ያደግንበት ፊውዳል ሥርዓት ነው። ልጅ በነፃነት ከወላጆቹጋር መነጋገር በማይቻልበት ሁኔታ ተቀርጾ ያሳደገን ሥርዓት ነው። ለዴሞክራሲ መታገል አለብኝ እያልክም ቢሆን ብዙ እንቅፋቶችያጋጥሙሃል። በአንድ በኩል በመሪዎች በኩል መሳፍንታዊ አስተሳሰብ አሁንም አለ። በሌላ በኩል ቅድም ያልኩት የተቋማት አለመኖርመሪዎች መስፍናዊ አስተሳሰብ ቢኖራቸው እንኳን የመሪዎችን መጥፎ ባህሪ መግታት ይችሉ ነበር። ለምሳሌ በአሜሪካ ዶናልድ ትራምፕመጥፎ ባህሪ ቢኖራቸውም ዴሞክራሲያዊ ተቋማት ስላሉ የትራምፕን ባህሪ መግታት ይችላሉ። ወደ እኛ አገር ስታመጣው እነዛተቋማት የሉንም። ይህ ደግሞ በአጭር ጊዜ የምትገነባው አይደለም። የረጅም ጊዜ ሥራ ነው። ይህ በመሆኑም አሁን ወደዛ ለመሄድሽግግር ላይ ነን ማለት ይቻላል። ያም ሆኖ ለስልጣናቸው ብቻ የሚያስቡ መጥፎ ሰዎችም አሉበት። ነገር ግን ያደግንበት ማኅበረሰብ እናየደሞክራሲ ተቋማት አለመኖር እነዛን መጥፎ ሰዎች ይገቱ ነበር። አሁን ችግሩ ምን መሰለህ? በሚነሱ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሰፋፊውይይት አናደርግም። ለምሳሌ “የትግራይ የበላይነት አለ” የሚል ነገር አለ። መኖሩም ሆነ አለመኖሩ እኮ በግልፅ ውይይትአይደረግበትም። በድብቅ አለ ይባላል። ነገር ግን የትግራይ የበላይነት መኖሩም ሆነ አለመኖሩ በግልፅ በቴሌቪዥን (ለምሳሌ በኢትዮጵያቴሌቪዥን) ግልፅና ዴሞክራሲያዊ ውይይት ቢካሄድበት እውነታው ታውቆ ይታረም ነበር። ነገር ግን ይህ አልተካሄደም። ስለዚህሁሉም ኋላ ቀር የሆኑ አስተሳሰቦች ዴሞክራሲያዊ ከባቢ በሚኖርበት ብዙ ጊዜ በኢህአዴግ ጠባብነት እና ትምክህት የሚሉ ነገሮችመልስ ያገኛሉ። ነገር ግን በመጀመሪያ የኢህአዴግ ፀረ-ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰቡ “ጠላት” ብሎ መፈረጁ ነው። ጠባብነትና ትምክህትግን አርሶአደሩም ጋር አለ፣ ላብአደሩም፣ ባለሀብቱም ውስጥ አለ። ከራሱ ከኢህአዴግ ውስጥም አለ። ለዛ ነው ኢህአዴግ “ጠላት” ሲልእኔ የምጠላው።
ሰንደቅ፡– ሰውን በአስተሳሰቡ ጠባብና ትምክህት ብሎ በጠላትነት መፈረጅ በራሱ የጠባብነትና የትምክህተኝነት ባህሪ ነው ብሎ መውሰድ ይቻላል?

ጄኔራል አበበ፡

–  ይህ ፀረ-ዴሞክራሲያዊነት ነው። በጣም ያሳስታል። ምክንያቱም ኅብረተሰቡ ውስጥ ብዙ የማይመቹ አስተሳሰቦችአሉ። እነዚህ አስተሳሰቦች ሲመጡ “ጠላት” ብለህ ከፈረጅከው ያለህን ጉልበት በሙሉ ተጠቅመህ ትዋጋለህ ማለት ነው። አሁን ግን እሱአይደለም መሆን ያለበት። አንተ ያላመንክበትን ሁሉ “ጠላት” ካልከው ጠቅላላ የዴሞክራሲ “ሀ-ሁ” የለም ማለት ነው። እሱ ደግሞትልቅ ችግር ነው። አሁን ካለንበት ቀውስ ለመውጣት መደረግ ያለበት ሕገ-መንግሥቱን መተግባር ነው። ዓለም ላይ ያሉ መብቶችንሁሉ ያካተተውን ሕገ-መንግሥት ተግባራዊ አድርገን መወያየት ባለመቻላችን ነው አሁን የገባንበት ቀውስ የተፈጠረው። ሕገ-መንግሥቱን መሠረት አድርገን ተወያይተን ወደ መፍትሄ ካልመጣን ግን የበለጠ አደገኛ ነው የሚሆነው።

ሰንደቅ፡– ሕገ – መንግሥቱ ይከበር ወይም ተግባራዊ ይደረግ ሥንል በውስጡ ያሉት መብቶች ሳይሸራረፉ ይጠበቁ ማለታችን ነው። ከሕገ – መንግሥቱ መብቶች አንዱ የመደራጀት ነፃነት ነው። በዚህ አንቀፅ መሠረት   የተደራጁ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ እንዳያቀርቡ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራትን ጀምሮ ሌሎች መብቶች ተጋፈናል። በተለይ  ለአሥር ወር በዘለቀው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ይህ የመብት ጥሰት ተደርጎብናል  ሲሉ ይናገራሉ። በዚህ መልኩ የተፈለገው ለውጥ መምጣት ይችላል?

ጄኔራል አበበ፡– አይመጣም። ግን ምንድን ነው ከአዋጁ በፊትም እኮ ያው የመብት ጥሰት ነበረ። በእርግጥ አዋጁ በወቅቱ የነበረውንችግር ለመፍታት አስፈላጊ ነበር። ፀረ-ዴሞክራሲያዊ የሆኑ አካሄዶች የነበሩት ግን ከአዋጁ በፊትም ነበር፤ በተለይ ከ1997 ዓ.ምበኋላ። በ1997 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሕዝብ ምን ማድረግ እንደሚችል ኢህአዴግ አየ። ከዛ ሁሉም የመንግሥት ተልዕኮ አስፈፃሚዎች(Missionaries) በሙሉ የሕዝብን መብቶች ለመንጠቅ ነው የተጠቀሙበት።

ሰንደቅ፡

– ከ1997 ምርጫ በኋላ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ያጠባሉ የተባሉ አዋጆች(የፕሬስ ሕግ፣ የፀረ ሽብር አዋጅ፣ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች አዋጅና የምርጫ ስነምግባር ሕግ) ወጥተዋል ሲሉ ሞጋቾች ያቀርባሉ። በዚህ ሁሉ የኢህአዴግ አመራሮች የጋራ ውሳኔ ሰጭነት ቀርቶ አቶ መለስ ሙሉ በሙሉ በሚያስብል መልኩ ወደፊት የቀረቡበት ጊዜ ነበርም የሚሉ አሉ። ወቅቱን የዴሞክራሲ ብርሃን   የጠፋበት የጨለማ ዓመታት ተብሎ ሊጠራ ይችላል?

ጄኔራል አበበ፡–  “የጨለማ ዘመን” የሚለው ተብራርቶ ካልቀረበ አስቸጋሪ ነው። ግን 1997 ዓ.ም አንድ የዴሞክራሲ ብልጭታነበር። ክስተቱ አገራችን ወደፊት የምትሄድበት ዕድል ነበር። ነገር ግን ያን ዕድል አጣነው። ያ ዕድል ያመለጠን በኢህአዴግ ብቻአልነበረም። ተቃዋሚዎችም ዝግጁ አልነበሩም። በእርግጥ ዋናው ተዋናይ ኢህአዴግ ነው። ያን ዕድል በማጣታችን ደግሞ ፀረ-ዴሞክራሲያዊነቱ እየባሰበት መጥቷል። በዚህ መልኩ ከሆነ እየተነጋገርን ያለነው የ1997 ክስተት አንድ ትልቅ የብርሃን ብልጭታ ነበር።

ግን ያን አጣነው። ነገር ግን ያን አጋጣሚ ከተማርንበት አሁንም ሌላ ዕድል አለን ብዬ አስባለሁ። ህዝቡ በሰላም የጠየቀውን ጥያቄመመለስ የሚችል ስልጣን በጉልበት መጠየቅ ጀምሯል። ስለዚህ ኢህአዴግ እንዳለፉት ጊዜያት ሕዝቡን እንደፈለገ ማድረግ አይችልም።

ቀጣዩ ምርጫም ተስፋ የምናይበት ይሆናል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። ምክንያቱም ኢህአዴግ እንደፈለገው ኮሮጆ የሚሰርቅበት አጋጣሚይኖራል ብዬ አልጠብቅም። ስለዚህ ከተጠቀምንበት ቀጣዩ ምርጫ ሌላ የብርሃን ብልጭታ የምናይበት ይሆናል።

ሰንደቅ፡– ቀጣዩ ምርጫ ሊካሄድ ሁለት ዓመታት ብቻ ናቸው የሚቀረው። አሁን አገሪቱ ውስጥ የፖለቲካው አየር መፋዘዝ ይታይበታል እየተባለም ይነገራል። በዚህ ፖለቲካ አየር ቀጣዩን ምርጫ የዴሞክራሲ“ብልጭታ” ያመጣል ብለን ተስፋ ማድረግ አንችላለን?

ጄኔራል አበበ፡– አሁን መመዘኛው እሱ አይደለም። መመዘኛው ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ ሕዝቡ ምን እያደረገ ነው የሚለው ነው።ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ሕዝቡ “አልገዛም” እያለ ነው። ይህ ደግሞ ለዴሞክራሲ መሠረታዊ ጥያቄ ነው። እኔም ተስፋየማደርገው በዚህ ነው። ኢህአዴግ ይፈልጋል፣ አይፈልግም አይደለም ጥያቄው። አሁን ያለው ሁኔታ ከኢህአዴግ ቁጥጥር ውጭ ስለሆነማድረግ ያለበት ብቸኛ አማራጭ የሕዝብን ፍላጎት መስማትና ከእሱ ጋር መሄድ ነው። ይህን ማድረግ ካልቻለ ሕዝቡ እንደማይገዛለትያውቀዋል፣ አይቶታልም።

ብዙ ሰው የሚመለከተው አሁን የተፈጠረውን የሕዝቡን አልገዛም ባይነት መጥፎ ጎኑን ብቻ ነው። እሱም የብሔር ግጭትየሚመስለውን ብቻ ነው። ነገር ግን ይህ ዘርን ለይቶ ማጥቃቱ ታርሞ የሕዝቡ አልገዛም ባይነት መጀመሩ ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባል።

አልገዛም የሚል ሕዝብ ማምጣት አስቸጋሪ ቢሆንም፤ ሕዝቡ ራሱ ያመጣው በመሆኑ ኢህአዴግ ሌላ አማራጭ የለውም። ወይ ስልጣኑንመተው፤ አለዚያ ሕዝቡ የሚለውን መስማት ይገባዋል።

ሰንደቅ፡– በተቃዋሚ ኃይሉ በኩል ያለውን በተመለከተስ?

ጄኔራል አበበ፡– የረባ ተቃዋሚ እኮ የለም። በእርግጥ የረባ ተቃዋሚ እንዳይኖር አንዱና ዋናው ምክንያት ኢህአዴግ ነው። ኢህአዴግይታወቃል፣ ጨቋኝ በመሆኑ ብዙ ነገር አበላሽቷል። በዚህም አሥቸጋሪ ፖለቲካ ፈጥሯል። ከዚህ በተጓዳኝ ግን ራሳቸው ተቃዋሚዎችምየራሳቸው ድክመት አለባቸው። ጠንካራ ተቃዋሚ ሁልጊዜ የሚታገለው በአሥቸጋሪ ሁኔታ ውስጥም ሆኖ እንጂ አልጋ በአልጋ በሆነሁኔታ ብቻ አይደለም። በራሳቸው መተማመን የላቸውም። ለዚህም ነው ብዙዎችን ተቃዋሚዎች “ተቃዋሚዎች” አይደሉም የምለው።

የተወሰኑ ጠንካራ ተቃዋሚዎች መኖራቸውን ግን አልክድም። እነሱም ቢሆኑም ግን በውስጣቸው ዴሞክራሲያዊ ባህሪ የላቸውም።

አይተማመኑም። ምንም እንኳን ኢህአዴግ ገንዘብና ስልጣን ስላለው የፈለገውን ማድረግ ቢችልም፤ ሁልጊዜ “ኢህአዴግ ነውየሚከፋፍለን” ማለት ከመጀመሪያውም አልነበሩም ማለት ነው። አሁን የተፈጠረውን የሕዝብ ሁኔታ እንኳን መጠቀም አልቻሉም።

በኦሮሚያ እና በአማራ ከተፈጠረው የሕዝብ ተቃውሞ ባልተናነሰ እንዲያውም በባሰ መልኩ በትግራይ ያለው ሕዝብ ወደ አመፅአልሄደም እንጂ ህወሓትን ከመጥላት አኳያ ሥናየው የበለጠ እንደሆነ ነው። ግን ይህን የሚጠቀምበት ተቃዋሚ የለም። ስለዚህእንደዚህ ያለ የተመቻቸ ሁኔታ ተቃዋሚዎች ተፈጥሮላቸው ነበር፤ አልተጠቀሙበትም እንጂ። በእርግጥ መንግሥት እየጨቆናቸውለመሆኑ ጥያቄ የለኝም ግልፅ ነው። ግን ትግል ነው እስካሉ ድረስ ይህን የሕዝብ መነሳሳት መጠቀም ነበረባቸው። በአጠቃላይበተቃዋሚዎችም ሆነ በኢህአዴግ በኩል ስታየው ፖለቲካችን ውስጥ ያለው ችግር ያመጣው መሆኑን ነው። በመሠረቱ ፖለቲካችንችግር አለበት።

ሰንደቅ፡– በአገሪቱ ከሚንቀሳቀሱ ሰላማዊ ፓርቲዎች አንዱ ኦፌኮ ነው። ይህ ፓርቲ ከሊቀመንበሩ  ዶር መረራ ጉዲና ጀምሮ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበሩ፣ ዋና ፀሐፊውና ሌሎች አመራሮቹ ታሥረውበታል። ፓርቲው   የመሪዎቹን እሥር ምክንያት የፖለቲካ አመለካከት እንደሆነ ነው የሚገልፀው። “በዚህ ሁኔታ ነው ያለሁት” የሚለውን ፓርቲ የትግል እንቅስቃሴ መተቸት ተገቢ ነው?

ጄኔራል አበበ፡– የፖለቲካ መሪዎች መታሰር በትግሉ ላይ ተፅዕኖ የለውም ማለቴ አይደለም። ግን አንድ ወይም ሁለት አመራር ታሰሩብሎ ትግል ማቆም ከመጀመሪያውም ድርጅቶቹ አልነበሩም ማለት ነው። እንደነገርኩህ መንግሥት ጨቋኝ (Impressive) ነው። ግንበዚህ ጨቋኝ ሥርዓት ውስጥ ሆነህም መታገል እስከመረጥክ ድረስ ልታደርግ የምትችለው የተፈጠረልህን የሕዝብ ድጋፍ ተጠቅመህመታገል ነው። ኦፌኮ ያልከው ፓርቲ እኮ ኦሮሚያ ውስጥ ሁሉ ሕዝብ በመንግሥት ላይ አልገዛም ብሎ ተነስቶለታል። ሕዝቡ እኮአምጿል፤ እንዲያውም አንዳንድ ቦታማ ጠብመንጃ እስከማንሳትም ደርሷል። ስለዚህ ፓርቲው ጠንካራ ከሆነ ምንም እንኳን መሪዎቹመታሰራቸው ቢጎዳቸውም ይህን እድል በሚገባ መጠቀም አለባቸው። በእርግጥ በዚህ መሀል ብዙ ወጣት ምሁራን በመታየታቸውእነዛን ወጣቶች በማቀፍ መሥራት ይቻላል። ዴሞክራሲያዊ የሆነውን ሕገ-መንግሥት መሠረት አድርገን ሕዝቡ ውስጥ ከሰራን ሰላማዊበሆነ መንገድ ማሸነፍ እንችላለን። በደርግ ጊዜ ይህ አይቻልም ነበር። ምክንያቱም ሕገ-መንግሥቱ በራሱ ፀረ-ዴሞክራሲያዊ ነበር።

አሁን ምንድነው መሰለህ? ይህ የእኛ ትውልድ ያበቃለት የሞተ ትውልድ ነው። ላለመሞት ይንገዳገዳል እንጂ የሞተ ትውልድ ነው።

አሁን ከላይ ያሉት ህወሓት ውስጥ ያሉት አመራሮች ለምሳሌ ላለመሞት ይንገዳገዳሉ እንጂ  የሞተ ትውልድ ነው። ሰው ሲሞትከመሞቱ በፊት ይንፈራገጣል አይደል? በዛ ትውልድ አመራር እየሆነ ያለውም ያ ነው። ስለዚህ በአገራችን እየሆነ ያለውን በተመለከትንጊዜ ሊያድናት የማችለው ወጣቱ ብቻ ነው። ግን ደግሞ ወጣቱ አልተደራጀም። ሽማግሌውም አልቻለም፤ ወጣቱም አልተደራጀም በዚህመሀል ፖለቲካዊ ቀውስ አለ።

ስለዚህ በተለይ ወጣቱ ምሁር በደንብ መዘጋጀትና መደራጀት አለበት። በተወሰነ ደረጃም ኦሮሚያ ውስጥ የሚታየው እሱ ነው። አሁንየኦሮሚያ ፕሬዝደንት አቶ ለማ የሚናገረው ነገር ወደ ተግባር ሲቀየር ምን ሊሆን እንደሚችል በኋላ የሚታይ ቢሆንም  ምርጥ ምርጥየሆኑ ሃሳቦች ያቀርባል። ፕሬዝደንት ለማ የሚያቀርበውን የመሰለ ሃሳብ እኮ ሌሎቹ አያቀርቡም። ሌሎቹ እኮ በራሳቸው ግምገማ፤በራሳቸው ጥልቅ ተሃድሶ በሚሉት ወንጀለኛ አስተሳሰብ ጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ ገብተው ነው የወጡት።

የአቶ ለማ አስተሳሰብ በተግባር ስናየው ሌላ ሊሆንም ይችላል ወይም ደግሞ ጥሩ ሊሆን ይችላል። መለካት የምንችለው በአሁኑ አቋሙስለሆነ ወጣቱ ትውልድ ይህችን አገር ይምራት ለምለው ሃሳቤ እሱ ምልክት ነው።

ሰንደቅ፡– ከወራት በፊት በትግርኛ ከሚታተም መፅሔት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ወጣቱ ምሁር ካረጀው አመራር ላይ በስልት ስልጣኑን መረከብ አለበት ብለው ነበር። በዚህ ሀሳብዎ ላይ የሚነሱ አስተያየቶች አሉ። ሃሳብዎ ሥርዓቱ ታድሶ እንዲቀጥል ነው? በሌላ በኩል ደግሞ በስልት ስልጣኑን መንጠቅ ሲባል እንዴት ነው የሚነጥቀው?

ጄኔራል አበበ፡– ጥያቄው እኮ የትኛው ነው የሚታደሰው? የሚለው ነው። በነገራችን ላይ ተሃድሶ የሚለውን ነገር ኢህአዴግአጨማልቆታል፤ አልወደውም። እኔ የምለው ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱ እንዲጠናከር ነው። የሚያጠናክረው ደግሞ የዴሞክራሲያዊትውልድ ነው። የእኛ የ60ዎቹ ትውልድ የፊውዳል አሥተሳሰብ እና ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ይዞ በመሃል እየጠፋ ያለ ትውልድ ነው።አሁን ያለው ትውልድ ግን ቢያንሥ ስለዴሞክራሲ ገና ከመጀመሪያ ደረጃ ጀምሮ ተምሯል። ስለ ሕገ-መንግሥት ያውቃል፤ የአሜሪካንምርጫ ያያል፤ የሌሎች አገራትንም ያያል። በእኛ አገርም ቢሆን ችግር ቢኖርበትም እንኳን ምርጫ ያያል። ችግር ቢኖርበትም እዚሁአገርም ጋዜጦች አሉ። ቴሌቪዥን ያያል። በዚህ መልኩ ነው ያደገው። በእኛ ጊዜ ግን ይህ ሁሉ አልነበረም። እኔ ራሴ ከመቀሌ ከመጣሁበኋላ ነው ቴሌቪዥን ያየሁት።

ይህ ትውልድ ግን ገና ሲያድግ ሳይፈልገው ነው ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ እየገባበት ያደገው። ይህ ትውልድ ገና ስላልተደራጀ ችግርአለበት።  ለመደራጀት ትንሽ ጊዜ ያስፈልገዋል።

ይህ ሥርዓት ይታደሳል፣ አይታደስም? የሚለውን ለማየት የሚታደስ እንኳን ቢሆን ሊታደስ የሚችለው በወጣቱ ትውልድ እንጂ አሁንባሉት ኋላ ቀር ሽማግሌዎች አይደለም። ይህ ችግር ከህወሓት ብቻ ሳይሆን ከብአዴንም ያለ ነው። በአንፃራዊነት ደኢህዴን እና ኦህዴድትንሽ ይሻላሉ። እዛም እዚህም ቢሆን የሚታደሰውና ይህችን አገር የሚያድነው ወጣቱ ትውልድ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ስልጣን“መንጠቅ” ሲችል ነው። ስልጣን ላይ ያለ ሰው ስልጣኑን አይሰጥም። ስለዚህ ወጣቱ ስልጣኑን መንጠቅ ነው ያለበት። ካልሆነ ግንበልመና አይሰጠውም።

አሁን ባለው ሁኔታ ወጣቱ ስልጣኑን ከሽማግሌዎች ላይ በሰላማዊ መንገድ መንጠቅ የሚችልበት ምቹ ሁኔታ አለ። ምንም እንኳወደተሳሳተ መንገድ ሊያመራ የሚችል የሕዝብ አመፅ ቢኖርም፤ ሕዝብ አልገዛም ማለት በመጀመሩ ይህን እድል መጠቀም ይችላል።

በእርግጥ እንደነገርኩህ በአንዳንድ አካባቢዎች የሕዝቡ አመፅ ከጎኑ ያሉ ሌሎች ኢትዮጵያውያንን እየጎዳ ነው። ይህ ክስተት አካሄዱሥህተት ቢሆንም፤ በአጠቃላይ ሲታይ ግን ሕዝቡ ጠያቂ እየሆነ መሆኑን ያሳያል።

ሰንደቅ፡– ሥልጣን ላይ ያለው ነባር አመራር ዴሞክራሲያዊ አይደሉም እያሉንነ ው። ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ የሌለው አመራር ዴሞክራት የሆነ ተተኪ ወጣት ሊያፈራ ይችላል ብሎ መውሰድ ይቻላል?

ጄኔራል አበበ፡– ምን መሰለህ በእቅድ አይደለም፤ በአጋጣሚ (Default) ነው። ደጋግሜ እንደነገርኩህ ዴሞክራሲያዊ የሆነ ሕገ-መንግሥት አለ። በሕገ-መንግስቱ መሠረትም ፓርቲዎች ሲቋቋሙ ታያለህ። ወጣቱ ከመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ጀምሮ በሲቪክስናየሥነምግባር (ሥነዜጋ) ትምህርት ስለ ዴሞክራሲ፣ መብት እና ፖለቲካ ተምሯል። ከዛ ባይማር እኮ በዕለት ተዕለት ህይወቱ የሚታየውአስተምሮታል። የ1997 ዓ.ም ምርጫ አንድ ትልቅ አስተማሪ ነው። ምንም እንኳ ትንሽም ቢሆን ሰንደቅን ጨምሮ ሪፖርተር፣ አዲስአድማስ ጋዜጦች አሉ። ከእነዚያ እያነበበ ወጣቱ ይማራል። ለዚህ ነው በእቅድ (Design) አይደለም በዲፎልት ነው የምልህ።

በዲዛይን ቢሆንማ አይወድቅም። ኢህአዴግ ሳያስበው የሠራቸው ብዙ መልካም ሥራዎች አሉ። ለምሳሌ ጥራታቸው ላይ ችግርቢኖርበትም ዩኒቨርስቲዎች ተስፋፍተዋል። የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶችም በየቀበሌውና ወረዳው ተከፍተዋል። ሌሎች መሠረተልማቶችም እንዲሁ። እሱ (ኢህአዴግ) በሄደበት መንገድ የማይሄድ ደሞክራቲክ ትውልድ እየተፈጠረ ነው።

ሁልጊዜ አንድ አመራር ወይም መንግሥት ሲያረጅ የሰራውን ጥሩ ሥራ እያበላሸ ይሄዳል። ለምሳሌ ድህነትን በመቅረፍ አኳያ ኢህአዴግጥሩ ነገር ሰርቷል። ይህ ግን ከሕዝቡ ጋር ካልሄደ መቃብሩ ነው የሚሆነው። ምክንያቱም ኢህአዴግ ቢፈልግም ባይፈልግም ዴሞክራቲክማኅበረሰብ እየተፈጠረ ነው። ኢህአዴግ ከዚህ ለውጥ ጋር መራመድ አቃተው። ይህ ደግሞ ተፈጥሯዊ ነው። በእኔ አመለካከትኢህአዴግ እስከ 1987 ዓ.ም ብቻ ነበር አገርን የማስተዳደር ኃላፊነቱን የተወጣው። ከዛ በኋላ ማድረግ የነበረበት “እኔ አልችለውምየሚችሉት የተማሩት ወጣቶቹ ናቸው፣ ቀስ በቀስ ስልጣኑን ያዙ” ማለት ነበረበት። ግን ድንቁርናም ተጨምሮበት እኔ ሁልጊዜእችለዋለሁ የሚል ነገር መጣ። ያም ሆነ ይህ ግን አሁን ኢህአዴግ ፈለገም፣ አልፈለገም ይህችን አገር ወደፊት መምራት የሚችል ምሁርአለ። ፈለገም፣ አልፈለገም ኅብረተሰቡ አልገዛም ማለቱን ሊረዳ ይገባል።¾

ለሰንደቅ ጋዜጣ ከሰጡት ቃለ መጠይቅ የተወሰደ