ከጥቂት ወራት በፊት የተከበሩ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዘዳንት አቶ ለማ መገርሳ “አዉሬዉን አቁስለነዋል!” ሲሉ የተናገሩትን ደግሞ ደጋግሞ የሚያስታዉሰኝ አንድ አብሮ አደጌ ዛሬም ዓይን ዓይኔን አተኩሮ አየተመለከተ…. “ያለህ አማራጭ መጨረስ ብቻ ነዉ!!….. አዎን ሌላ አማራጭ የለህም!!….. ያለህ ብቸኛ አማራጭ ያቆሰልከዉን አዉሬ መጨረስ ብቻ ነዉ። አዝነህ ወይም ተዘናግተህ ትንፋሽ ይወስድ ዘንድ ከፈቀድክ እርሱ አዉሬ ነዉና የአንተ መጨረሻህ በፍፁም አያምርም!” ሲል በቁጣ ሲናገር የሚሰማዉ ሌላ ሰዉ ከእኛ ጋር ቢኖር እኔን አቶ ለማ መገርሳ መሆን አለባቸዉ ብሎ ይጠረጥር ነበር። ለነገሩ እኔና ስንታየሁ ብቻችንን ነበርን።
የቀድሞ ጓደኛችንን ተክላይንም ማዕቀብ አድርገንበት ከተለየነዉ በርካታ ሳምንታት አልፈዋል። ምንም እንኳ ኋላ ቀርነት ቢመስልም ወገናችንን እንደ ወባ ቀፍድዶ ከያዘ የትግሬ ቡድን ጋር በምንም መልኩ የሚዛመድ ወይም የሚተባበር ለጊዜዉም ቢሆን የእኛ ቡና አጣጪ ሊሆን አይችልም ብለን ወስነን በግልፅ ነግረን ከድል በኋላ እንገናኝ ብለን አባረነዋል። በእርግጥ ከእኔና ከስንታየሁ የሚቀዳ ቁምነገር ሊኖር ባይችልም የዘረኞቹና የአዉሬዎቹ ዘመዶቹ መንፈስ አጠገቡ ይኖራልና ማባረሩን መርጠናል። በነገራችን ላይ ትግሬ ላይ ብቻ ሳይሆን የትግሬ ስሞችንም የያዘ ምንም ዓይነት ዕቃ ላንገዛ እኔና ስንታየሁ ቃል ተገባብተናል። እነሱ በአንድ ለአምስት ቀፍድደዉ ተጫዉተዉብን ነበር…….እኔና ስንታየሁም ከወራት በፊት አንድ ለሁለት ብለን ወስነንባቸዋል። በቃ!!….. አዎን በቃ ማለት ከዚህ ይጀምራል። እስኪ እናንተም ሞክሩት። ከአንድ ወይም ከሁለት የቅርብ ጓደኞቻችሁ ጋር ብቻ ሆናችሁ ‘ትግሬም….. የትግሬም ቁሳቁስ ለምኔ’ ብላችሁ ቃል ተገባቡ ….
ወደ ኦህዴድና ስንታየሁ ልመለስ…
ስንታየሁን የማዉቀዉ ለረዥም ዓመታት ቢሆንም አንዳንዴ ግን አዲስ ይሆንብኛል። የዛሬዉም ሁኔታዉ ለበርካታ ሰዓታት እንዲገርመኝ አድርጓል። ዓይኖቹን አፍጥጦና…. እጆቹን እያወናጨፈ ሲናገር ልክ የኦሮሞ አልያም የአማራ ፓሊስ ልዩ ኅይሎችን ሰብስቦ ጥብቅ መመሪያ የሚሰጥም ይመስል ነበር…..”ይህ ሁሉ መንበርከክ ምንድን ነዉ?…. ጠቅላላ ትግራይን አስጣጥቆ ኦሮሞ ክልል ቢመጣ እዚህ ግባ የማይባል ቁጥር ያለዉ ባንዳና የባንዳ ዘር ማንዘርን ይህ ሁሉ ማስታመም ለምንድን ነዉ?….. ይህ የባንዳ ርዝራዥ የተወለድንበት መንደር ድረስ ገብቶ መሳሪያ ሲያስፈታንና ሱሪ ሲያስወልቀን በለቅሶ ወደ ገደል የምንፈረጥጠዉ ምን ነክቶን ነዉ?….. እጅ ባይኖረን በጥርሳችን ዘልዝለን ደማቸዉን ማፍሰስ እንዴት ያቅተናል። ፓሊስህን ያሰረ ሌባ ቀጥሎ አንተን ይገድልሃል። ይህ የታወቀ ነዉ። መሳርያ ተሸክሞ ሱሪዉን ለሚያወልቅ ሙት እስረኛ መፈታትን የሚለምን እይኖርም። ስለዚህ በቃ በል!!” ሲል ብዙ ተቆጣ። ለነገሩ የቅርበታችንም ዋና መሰረቱ እንዲህ በረዥም ጊዜ አንዴ ብቅ የሚለዉ ያመረረ ቁጣዉና አትንኩኝ ባይነቱ ነዉ።
ያኔ ወያኔ አዲስ አበባ ሲገባ እኔም ስንታየዉም ከብላቴ የአየር ወለድ ማስልጠኛ ካምፕ ወጥተን እጃችንን ለወንበዴ አንሰጥም በማለት ወደ ኬንያ ለስደት ከበርካታ የአየር ወለድ ጀግና የሰራዊቱ አባላት ጋር እየተጓዝን ነበር። በጦር ካምፕ ዉስጥ በስልጠና ላይ እያለን በዕፍት ቀናት አልያም በምግብ ሰዓት አልፎ አልፎ በርቀት ከመተያየት በስተቀር ብዙም አንተዋወቅም ነበር። ኤኬ 47 ጠመንጃ አንግበን ወደ ኬንያ እናመራ በነበረበት ለሊት ግን ደጋግሞ ይናገረዉ የነበረዉ ቁጣ የተቀቀለዉ ንግግሩና ማሳሰቢያዉ መቼም ከሕሊናዬ ላይጠፋ ተመዝግቦ ቀረ……”ምንድን ነዉ ይህ ሁሉ ሩጫ? ….. ምንድን ነዉ መረጋጋት ብሎ ነገር?……መጓዝ የነበረብን ወደ ትዉልድ መንደራችን ድረስ ከነቅጫሞቻቸዉ የመጡትን ወንበዴዎች ለመቅጣት መሆን ሲገባዉ እኛ በሌላ አቅጣጫ ወደ ሌላ ሰወ ሀገርእንፈረጥጣለን። ጥለን እንውደቅ …. “ ብሎ ደጋግሞ ሲናገር ብዙዎች ግን ‘ስልታዊ ማፈግፈግ ይሻላል’ ብለዉ ትኩስ ወኔዉን አቀዝቅዘዉ ለስደት ዳረጉት።
ስደት ላይም በጣሙን ተግባባን…. ተዋወቅንም። ሁለታችንም ገና አፍላ የኮሌጅ ተማሪ ዘማቾችና ዘር የማንጠያየቅ የአንዲት ኢትዮጲያ ልጆች ስለነበርንም ወንድማማች ሆንን።
የወንድሜ ስንታየሁ የዛሬ ጠዋቱ ቁጣ በትዝታ ወደዚያ የስደት ጉዞ ለሊት ወሰደኝና ለኦህዴድ ፈራሁ። አዎን!….ኦህዴድ ያለዉ ብቸኛ ጥሩ አማራጭ ‘የቆሰለ’ ያለዉን አዉሬ መጋፈጥ እንጂ ወደየትም መሰደድ ወይም ማጎብደድ አይደለም። ፈሪና አዉሬ ጨካኝ በመሆኑ የቆሰለ የተባለዉ አዉሬ ያገግም ዘንድ ከሆነ ትግሬ የኦህዴድ ቀባሪ ይሆናል።
‘አምላኬ ሆይ ጠላቴን ከእግሬ ስር ይሁን’ እንዳለዉ ዳዊት … ጌታ ሆይ ለኦህዴድም ይደረለት።

