12/03/2018

የትግራይ ነጻ ኣዉጪ ፋሽስት ጦር ሞያሌ ዉስጥ የከፈተዉን ጭፍጨፋ በማምለጥ የኢትዮጵያን ድንበር በማቋረጥ ወደ ኬንያ ግዛት የገቡትንና ቁጥራቸዉ ወደ 10 ሺህ የሚጠጉትን የሞያሌ ስደተኞች የአስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸዉ መገለጹ ይታወቃል።
በመርሳቤት ምክትል ገዢ ጉቦ ጨዌ የተመራ ቡድን፤ የሞያሌ ኬንያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኣባል ቃልቻ ጉፉና የኣለም ኣቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ኣባላት ያሉበት ቡድን ስደተኞቹ ያረፉበትን መጠለያ ጎብኝቷል።
በገዛ ሃገራቸዉ የመኖር ህልዉናቸዉን ተነፍገዉና ከጭፍጨፋ በማምለጥ ወደ ጎሬቤት ሃገር የሽሹትን ዜጎች የጎሬቤት ሀገር ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና የግብረ ሰናይ ተቋማት ወደ ተጠለሉበት ስፍራ በመሔድ ጎብኝተዋል።
የአካባቢዉ የኬንያ ባላስልጣናት ላሳዩት ስብአዊ ትብብር መላዉ የኦሮሞ ህዝብ ከልብ ያመሰግናል።