✍ፍፁም አየነው

በሀገራችን ኢትዮጵያ የተለያዩ የህዝብ አስተዳደሮችም ሆነ የተለያዩ አደረጃጀት ተፈጥረዋል፡፡በእነዚህ ውስጥ አንዱ የብሔረሰብ አደረጃጀት ነው፡፡ዘርን መሰረት በማድረግ ሀገራችን ውስጥ ካሉ ብሔረሰብ ያልተደራጀ የለም ማለት ይቻላል፡፡በፓለቲካ ድርጅትነት ያልተደራጀ ቢኖር እንኳን በማህበር ተሰባስቧል፡፡ከእነዚህ ውስጥ በዕድሜ አጭሩ ነገር ግን በፍጥነቱ አስደማሚ የአማራ ብሔርተኝነት ነው፡፡የአማራ ብሔርነትነት ታዲያ ከሌላው ብሔርተኞች የሚለየው አንድን ህዝብ ጠላት አድርጎ አለመነሳቱ እና በበደል ግፊት የተፈጠረ መሆኑ ነው፡፡አብዛኛዎቹ ሌሎቹ ብሔርተኝነት በስርዓት ላይ ተመርኩዘሁ መሆኑ ቀርቶ አንድን ህዝብ(አማራን) ባልዋለበት በፈጠራ መታገያና በጠላትነት ፈርጀው ነው የተመሰረቱት፡፡ ከአንድነት አደረጃጀት ውስጥም በዚህ አይነት መልኩ የተደራጁ ከሩቆቹ እስከ ቅርብ ጊዜዎቹ ማንሳት ይቻላል፡፡ለአሁን ዋናው ትኩረቴ የአማራ ብሔርተኝነት ግንባታ ላይ ነው፡፡ይህ ብሔርተኝነት ፋሽን ሆኖ የተጀመረ አይደለም በመራራ ዋጋ እንዲጀመር የተገደደ እዚህ ለመድረስም ትልቅ መሰዋዕነት የተከፈለበት የአማራው የዘሩ መቀጠያ ድልድይ ነው፡፡


የአማራ ብሔርተኝነት ትግል የአማራ ነው ሌላው ሊያስጨንቀው አይገባም ጠላቱ ሆኖ እስካልተሰለፈ ድረስ ፤ለዛውም እኔ አማራ ነኝ የሚል ወገን የፈጠረው ነገር ግን ሁሉንም አማራን የሚታደግ ትግል ነው፡፡
ይህ አደረጃጀት በጥርጣሬ እና በፍርሀት የሚመለከቱ መልካም እይታ እና ወገናዊነት ከተሰማቸው ሊረዳቸው ሊያምኑበት ይችላላሉ፡፡ትግሉም ጨለምተኛም አይደለም፡፡

የአማራ ብሔርተኝነት የአማራ ህዝብ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቱ ሳይጠበቅ መልስ አግኝቷል ማለት አይቻልም፡፡በድህረ ወያኔም የአማራ ህዝብን ዘለቄታዊ የአንድነት ትስስር የመረዳጃ የትግል መስመርም ይሆናል፡፡እንደ እኔ እይታ ይህ የትግል አደረጃጀት ካሉበት እንቅፋቶችና የስኬት ፍጥነት አንፃር ለሚጎትቱት በእነዚህ በተረዘርኳቸው ነጥቦች ላይ አመርቂ ውጤት ሊኖረው ይገባል፡፡

፩ኛ – ብቃት ያላቸው መሪዎችን መፍጠር
-ይህ መሰረታዊና የትግሉ ቁልፍ አካል ሲሆን አሁን ካለው በላይ በሁለገብ ሙያዎች የታቀፈ የአማራ ምሁራን ተሳትፎ በህብዑም ሆነ በግልፅ በቅርቡ ባለ አደረጃጀት ውስጥ መታቀፍ አለበት፡፡ያለ ቁርጠኝነትና ብቁ አመራር ትግሉ ስምረት አይኖረውም፡፡በዚህ ሂደት ውስጥ የግለሰቦቹ ተነሳሽነት ብቻ ሳይሆን አሁን ባሉ አደረጃጀቶች ግፊትና እንቅስቃሴ ጉልህ አስተዋፅኦ ሊኖረው ይገባል፡፡ጠንካራ አደረጃጀቶች ብቁ መሪዎችን ፤ብቁ መሪዎች ደግሞ አደረጃጀቶችን ማጠንከር መሰረታዊ ተግባራቸው መሆን ይኖርበታል፡፡መሰዋዕነትነት ለመክፈል የተዘጋጀ፤ ሃላፊነትን የሚቀበል መሪ መፍጠር ይገባል ያለ እነዚህ ስኬት አይመጣም፡፡

፪ኛ- የስነ ልቦና ጥገናና ዝግጁነት
– አማራ በዕሴቶቹ ስነ ልቦናውን ሚገነባባቸው ባህላዊ የሆኑ ልምዶቹን(ጃሎ ፣ስለላ ፤ቀረርቶ ፣ፉከራ) እንዳሉ ሆነው ያሉ አደረጃጀቶች ሁሉ ህዝቡ ላይ ስርዓቱ የነዛቸውን የማሸማቀቂያ እና የሞራል ድቀቶች በማህበረሰቡ ላይ የማንቃት ስራ መስራት ይኖርባቸዋል፡፡ለዚህ ያሉ የሚባሉ አማራጮች ከማህበራዊ መገናኛ ዘርፎች እስከ ኤሌክትሮ ሚዲያዎች በመጠቀም መስራት ይቻላል፡፡በተለይ ከአማራ ጥንተ ግዛቶች ውጭ የሚገኙ አማራዎች እና በሰፊው ወያኔ በአማራ ላይ ማህበራዊ ምህንድስና የሰራበት የሸዋ ክፍለ ሀገር ዋነኛው የትኩረት ነጥብ ነው፡፡ዛሬ በምናካሂደው የአማራ ብሔርተኝነት ከፍተኛ ትኩረት ያልተሰጣቸው ከአማራው አካባቢ ውጭ ያሉ አማራዎች እና የአማራ ደም ያለባቸው ነገር ግን ከአማራ አካባቢ ውጭ የተወለዱ ባህሉንም ቋንቋውም ሳያውቁ አማራነት ብቻ ሚሳደዱ ወገኖች ናቸው፡፡በእነዚህ አይነት ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመረዳት ወይ እነሱን ሆኖ መገኘት አልያም ጉዳት መረዳትና መስራት ያስፈልጋል፡፡በአንድ ጀንበር ያልተጎዳ ህዝብ በአንድ ጀንበር ከችግሩ አይላቀቅም፡፡በማንኛውም አማራጮች በትኛውም አደረጃጀት የዚህ ብሔርተኝነት አቀንቃኝ ከጠላቱ የተሻለ የስነ ልቦና የበላይነት መያዝ አለበት፡፡

፫ኛ -ፓለቲካዊ ንቃት ብሔርተኝነቱን በተመለከተ
– የፓለቲካ ንቃት በእየጊዜው ሊዳብርና ሊሻሻል እንደሚችል ሁሉ በዚህ ብሔርተኝነት ምህዋር ውስጥ የሚንቀሳቀስ ሁሉ ወጥና ተቀራራቢ ንቃት ሊኖረው ይገባል ስለሚታገለው ትግል፡፡ዘመናዊ ትምህርት ከተባው እስከ መለኮታዊ አተምሮ የተጠበበው ብሎም በመካከለኛ የትምህርት ደረጃ የሚገኘውም ሆነ ያልተማረው አርሶ አደሩ ስለሚታገለው ትግል መነሻ እና መድረሻ ጠንቅቆ ሊያውቅ ይገባል፡፡አለበዚያ ግን የዕውቀት ክፍተት የትግል ክፍተት ይፈጥራል፡፡በሙሁራን በኩል በዚህ ዘርፍ ከሌላው በተለየ መሬት የመረደ እንቅስቃሴ በማድረግ ክፍተቶችን በመድፈን አናፂ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡በሚታገሉት ትግል አደረጃጀት የሚኮሩ ፣የማይሸማቀቁ የሚታገሉለትን ህዝብና ጥቅም የሚያስከብሩ መሆን መቻል አለባቸው፡፡
በየትኛውም መንገድ ስለ እዚህ እውነተኛ ትግል ማስረዳት የሚችል ግንዛቤ መኖር አለበት፡፡

፬ኛ ጠንካራ የሰራዊት ግንባታ
– ብቁ መሪ ፣የስነ ልቦና ዝግጁት እና በተገነባ የፓለቲካ ንቃት መሰረት እና መመዘን የሚችል በአንድ ዕዝ የሚመራ ሰራዊት የትግሉ ዋስትና ነው፡፡ተቆርቋሪ እና ተከላካይ የሌለው ህዝብ ከጥፋት ሊከላከልተለት የሚችል መንገድ የለም፡፡የአማራ አደረጃጀት ሁሉ ትኩረት ሊያደርግበት የሚገባ የከበረ ጉዳይ ነው፡፡ጉልበት የሌለበት ፓለቲካ ምን ቢሆን ለድል ሩቅ ነው ፤እንደ አማራ ህዝብ ትግል ደግሞ ሰፊ ጉዳት ይኖረዋል፡፡ሚተኩስ ጠላት ይዞ በባዶ እጅ መታገል የዋህነት ከመሆን አልፎ ከአማራ የጥፋት ዘመኖች ውስጥ ሊመደብ የሚችል ትልቅ ጥፋት ያመጣል፡፡ ብቁና ሁለገብ ሰራዊት እና በአንድ የመስመር ፍሰት የሚወርድ የመረጃ እና ደህንነት አሰራር ሊኖረው ይገባል፡፡በዚህ ነጥብ ወደ ፊት በደንብ በሰፊው እመጣበታለው፡፡

፭ኛ ህዝባዊ ድጋፍ
– ከላይ በተጠቀሱት ነጥቦች ላይ የወረደ ትግል ለድል ለህዝብ ቅርብ ነው፡፡የህዝብን ጥያቄን የሚመልስ ትግል የህዝብ ድጋፍን ያገኛል፡፡የህዝብ ድጋፍ ያለው ትግል ደግሞ ያሸንፋል፡፡አንባገነን የሆነ ስርዓት የመጀመሪያው ውድቀት የምሁራንን ተቀባይነት ማጣትና ተቃውሞ እና የህዝብ ድጋፍ ማጣት ነው፡፡

የህዝብ ትግል ሁሌም ትክክል ሁሌም አሸናፊ ነው!!!