የአልጀርሱን ስምምነት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለመተግበር ፣ እንዲሁም፣ የሀገሪቱን ግዙፍ የልማት ድርጅቶች በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ለግሉ ዘርፍ ክፍት ለማድረግ የኢሕአዴግ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ትናንት ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ሕዝቡን በሰፊው እያነጋገሩ ይገኛሉ።

«ብሔራዊ ዕርቅ እና የሽግግር መንግሥት ምስረታ መቅደም ነበረበት።»

የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የተለያዩ የህብረተሰቡ ክፍሎች የገዢው ፓርቲ፣ ኢሕአዴግ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እነዚህን አካራካሪ ያሏቸው ውሳኔዎች ላይ ከመድረሱ በፊት ሕዝብን ማማከር ነበረበት የሚሉ አስተያየቶች ሰንዝረዋል።

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ

አርያም ተክሌ

ሂሩት መለሰ

Source     –   DW