
መለስካቸው አምሃ (VOA)
በኢሮብ ወረዳ የደውሃን ከተማ ሕዝብ የአልጀርሱን ሥምምነት ተግባራዊ ለማድረግ የተወሰነውን ውሳኔ፣ በአደባባይ ተቃወመ፡፡አዲስ አበባ — በኢሮብ ወረዳ የደውሃን ከተማ ሕዝብ የአልጀርሱን ሥምምነት ተግባራዊ ለማድረግ የተወሰነውን ውሳኔ፣ በአደባባይ ተቃወመ፡፡ በተቃውሞ ሰልፉ የወጣው የከተማዋ ሕዝብ፣ የውሳኔው ተግባራዊነት፣ ለኢሮብ ሕዝብ ሕልውና፣ አደጋን እንደሚጋርጥ ተናገረ፡፡ ውሳኔው ኢ-ፍትሃዊ ነው ያለው ሕዝብ፣ ፍትሕ አልባ ሰላም ሊኖር አይችልም ብሏል፡፡ዛሬ ዘግይቶ የወጣ አንድ የሕውሃት መግለጫ፣ ሕዝብ ያላመነበት ውሳኔ ተግባራዊ እንደማይሆን ገልጿል፡፡
የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
