ሰኔ 3፤2010 ዓ. ም
የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ “የክልኩን እና የሃገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታ እገመግማለሁ” በሚል አስቸኳይ ስብሰባ እንደጠራ ለድርጂቱ ቅርበት አለው የሚባልለት የፋና ብሮድካስቲግ ኮርፖሬት ዘግቧል።
ድርጂቱ ስብሰባውን እንዳጠናቀቀ የገመገማቸውን ነጥቦች እና የደረሰበትን አቋም ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
ከባድማ ጋር ተያይዞ ገዢው ፓርቲ ሰሞኑን ያሳለፈው ውሳኔ ጋር የተያያዘ እንደሆነም ተገምቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከኡጋንዳ ወደ ግብጽ አቅንተው የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት በሚያደርጉበት ወቅት ነው የህወሓት ማአከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ የተጠራው። በዚህ ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የጦር ኃይሎች ኤታማዦር ሹሙን ሳሞራ ዩኑስን በጡረታ አሰናብተው በምትካቸው ጀኔራል ሰዐረ መኮነንን መሾማቸው ይታወሳል።
በተያያዘ ዜና ትላንት በኢሮብ ትግራይ የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከአስራ ስምንት ዓመት በፊት ከኤርትራ ጋር በአልጀርስ የተደረገውን የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመቀበል ባድመን ለኤርትራ አሳልፎ ለመስጠት የደረሰበትን ውሳኔ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ተደርጓል።


Ads by Revcontent
Oncologists Are Freaking Out After Officials Leak True Cause of Cancer
Natural Health Solutions
Men, Try This Tonight – It “Destroys” ED
World Health Labs
Fascinating Facts You Never Knew About Russia
OMG LANE
These Famous Last Words Will Stay With You Forever. #10 Will Blow Your Mind
OMG LANE
If You Come Across This Snake, Your Life Is All But Over
OMG LANE
Most Heroic Stories Of Animals That Will Leave A Lump In Your Throat
OMG LANE

Ads by Revcontent
