አቶ አብዲ ሞሃመድ
BBC Somali

የሶማሌ ክልልን ለአስር ዓመታት ገደማ ያስተዳደሩት አብዲ ሙሃመድ ዑመር ያለመከሰስ መብታቸው ተገፈፈ።

የሶማሌ ክልል ምክር ቤት ትላንት ባካሄደው መደበኛ ያልሆነ ጉባዔ ነው አብዲ ሙሃመድ ዑመርን ጨምሮ የሰባት አባላቱ ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ የወሰነው።

ምክር ቤቱ የግለሰቦቹን መብት ያነሳበት ምክንያት በቅርቡ በክልሉ ከተነሳው አለመረጋጋት ጋር ተያይዞ እንደሆነም አስታውቋል።

በሶማሌ ክልል በተከሰተ ቀውስ ህይወት ሲጠፋ አብያተ-ክርስትያናት ተቃጠሉ

የአባላቱን ያመለከሰስ መብት የማንሳት ውሳኔውንም ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ እንዳፀደቀው ነው የተገለፀው።

ከዚህ በፊት የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ሙስጠፋ ሙሀመድን ዑመርን የክልሉ ጊዜያዊ ፕሬዝደንት አድርጎ መሾሙ አይዘነጋም።

ክልሉን ለበርካታ ዓመታት የመሩትን አቶ አብዲ ሙሐመድ ኡመርን በመተካት ለሁለት ሳምንታት ክልሉን በፕሬዚዳንትነት ሲመሩ የቆዩት አቶ አህመድ አብዲ ሞሐመድ፤ አቶ ሙስጠፋ ጊዜያዊ ፕሬዚዳንት ሆነው እንዲቀጥሉ የፓርቲው ሕገ-ደንብ እንደሚፈቅድላቸው ገልጸው ነበር።

ሙስጠፋ ኡመር የሶማሌ ክልል ጊዜያዊ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾሙ

አብዲ ሞሃመድ ኡመር ከስልጣናቸው ወረዱ

አቶ አብዲ ስለተናገሩት ጉዳይ እንደማያውቅ ኢህአዴግ ገለፀ