December 10, 2018 

Sheger FM

ኢትዮጵያ በ27 አመት ውስጥ 36 ቢሊዮን ዶላር ወይም አንድ ትሪሊዮን 80 ቢሊዮን ብር ገደማ የሚገመት ሀብት ሸሽቶባታል፡፡

ይህ የገንዘብ አቅም ወይም የሀብት አቅም በ80 ቢሊዮን ብር ሂሳብ 13 የህዳሴ ግድቦችን ለመገንባት የምችል የገንዘብ መጠን ነው፡፡

በተደጋጋሚ የውጭ ምንዛሪ ከጓዳዋ የሚጎልባት፣ ከተሰበሰበውም የሚመነተፍባት ኢትዮጵያ በተለያየ ጊዜ በግፍ እና በተጋነነ ዋጋ ሀብቷ ከሀገር ሸሽቷል፡፡ ለአንድ ሀገር ጤናማ ኢኮኖሚ መኖርም የውጭ ምንዛሪን ማስተዳደር እና መቆጣጠር እንደ ዋና ስራ ይቆጠራል፡፡

ነገር ግን ቸልታው እየበዛ ቁጥጥሩም እየላላ በመቀጠሉ ይዞ የመጣውን ችግር አፍጥጦ እያየነው ነው፡፡

ተህቦ ንጉሴ ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ ሀብቷ በምን መንገድ ሲሸሽ ቆይቷል ? ይዞ የመጣውስ ችግር ምንድን ነው? ሲል የኢኮኖሚክስ ባለሙያ ጠይቋል፡፡