
On Dec 24, 2018 1,978 አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 15፣ 2011 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ኢትዮጵያን በውጭ ሀገሮች ለሚወክሉ አምባሳደሮች ሹመት ሠጥተዋል። በዚሁ መሠረት፡-
1. አቶ ዘነበ ከበደ
2. አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ
3. ወ/ሮ ሙሉ ሰለሞን
4. አቶ አብዱልአዚዝ መሐመድ
5. ወ/ሮ ናሲሴ ጫሊ
6. አቶ ሐሰን ታጁ
7. አቶ ረታ አለሙ
8. አቶ ሄኖክ ተፈራ
9. ወ/ሮ አለምፀሐይ መሠረት
10. ዶ/ር ትዝታ ሙሉጌታ
11. አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ
12. አምባሳደር ተሾመ ቶጋ
13. አቶ ተፈሪ ታደሰ
14. አቶ ፍፁም አረጋ
15. ዶ/ር አዲሱ ገ/እግዚአብሔር
16. አቶ ሚሊዮን ሳሙኤል
17. አቶ መለስ አለም
18. አቶ ብርሃኔ ፍስሐ
19. ዶ/ር አይሮራት መሐመድ
20. አምባሳደር ሳሚያ ዘካርያ
በባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደርነት ተሹመዋል፡፡
