January 13, 2019
ኢት-ኢኮኖሚ /ET- ECONOMY
ተፎካካሪ ፓርቲዎች የፖለቲካ ፕሮግራማቸውን ለህዝብ ማሳወቅ፣ ከአባሎቻቸው በሚገኝ መዋጮ መንቀሳቀስና 80 ፓርቲዎች ግፋ ቢል ወደ አራትና አምስት ፓርቲነት ተዋህደው መሥራት ይጠበቅባቸዋል፡፡ በብሄር የተደራጁ ፓርቲዎች ህብረት ፈጥረው መዋሃድ ብሎም እስከሚቀጥለው ምርጫ ዘመን ወደ ህብረ ብሄራዊ ፓርቲነት እንዲቀየሩና ወደ ልማት ማህበርነት እንዲቀየሩ ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡ በዜግነት ላይ የተመሰረቱ ህብረ ብሄር ፓርቲዎች ከብሄር ድርጅቶችና ፓርቲዎች ጋር በሠላማዊ መንገድ በውይይት ተቀራርበው በመስራት ለአለፉት 27 ዓመታት ወያኔ የተጠቀመበትን የዘር ፌዴራሊዝምን የከፋፍለህ ግዛ አንባገነናዊ አስተዳደር ቀስ ብለው ወደ ህብረ ብሄራዊ ፓርቲነት እንዲቀየሩ ማድረግና በክልሎች ማኃል ወያኔ ያካለለውን ድንበርና ወሰን የህዝብ መፈናቀልና ጦርነት ያስከተለ በመሆኑ በሰላማዊ መንገድ በሀገር ሽማግሌዎች እንዲፈታ በማድረግ ግጭቶችን ማስቀረት ሥራ መሥራት ይጠበቅባቸዋል እንላለን፡፡ ኢትዮጵያ የራሶ ድንበርና ክልል ብቻ እንዲኖራት በማድረግ በክልላዊ መንግስቶች ድንበርና ወሰን ሊኖራቸው አይገባም እንላለን፡፡
“Efforts to build strong, viable and democratic political parties have proven to be just as challenging as constructing formal and functioning institutions. There are multiple reasons for this. First, in developing countries in general and transitional environments in particular, parties are often poorly institutionalized and tend to be organized around narrow identity markers or personal relations. Commonly they only come to life during elections, and are seldom based on a clear ideology or political agenda (Reilly 2013). As a result, politics tends to be both highly personalized and strongly identity-based around whatever cleavages [sic]–tribe, language, regional or religion–is most salient”(Reilly 2013:90).These tendencies are often reinforced in war-torn societies, where authority is unclear and suspicion and fear permeate communities. Under such circumstances people are even more inclined to attach themselves to like-minded individuals or people who share similar traits (Burt 2005; Lyons 2005).“
“A second reason for the weakness of political parties in war-ridden societies is that the organizational structures of armed groups seldom function as a base conducive to building parties. In many civil wars, especially in an African context, militant organizations are created around the interest of one or several elites and their networks of dependents. Such organizations can best be likened to warlord enterprises, whose raison d’être is to further the political and economic interests of their leaders.“
ህዝባዊ ግምባር ሓርነት ኤርትራ (ህግሓኤ) ከሰላሳ አመታት የሽምቅ ውግያ በኃላ አስመራን ተቆጣጠሩ፣ህወሃት/ ኢህአዴግ መንግስት ከ17 አመታት የትጥቅ ትግል በኃላ በጋራ አዲሲ አበባን ግንቦት 20 ቀን 1983ዓ/ም ከተቆጣጠሩ በኃላ ሰላማዊ የሸግግር መንግስት የተወሰኑ ተቃዋሚ ብድኖችን (ኢህአፓ) በማግለል የሽግግር ቻርተር በማፅደቅ 86 አባላት ያሉበት የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች የተሳተፉበት የሽግግር መንግስት ምክር ቤት ተመሠረተ፡፡ የምርጫ ኮሚሽን ማssሚያ አዋጅ ተዘጋጅቶም በ1984ዓም የወረዳና የቀበሌ ጊዜያዊ አስተዳደር አካላት ምርጫ ተከናወነ፡፡ በግንቦት ወር 1984ዓ/ም የብሄራዊ፣ ክልላዊ፣ የዞን እና የወረዳ ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ተካሄደ፡፡ ለማጠቃለል የኢትዩጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ከተመሠረተ ጀምሮ በኢትዩጵያ አምስት ምርጫዎች ተከናውነዋል፡፡ አንደኛው በግንቦት 1987፤ሁለተኛው በግንቦት 1992፣ ሶስተኛው በግንቦት 1997፣ አራተኛው በግንቦት 2002፣ አምስተኛው በግንቦት 2007ዓ/ም ተከናዎኖል፡፡ እንዲሁም ስድስተኛው በግንቦት 2012 ዓ/ም ይከናወናል፡፡
At the federal level, Ethiopia elects a legislature. The Federal Parliamentary Assembly has two chambers: the Council of People’s Representatives (Yehizbtewekayoch Mekir Bet) with not more than 550 members as per the constitution but actually nearly 547 members, elected for five-year terms in single-seat constituencies; and the Council of the Federation (Yefedereshn Mekir Bet) with 117 members, one each from the 22 minority nationalities, and one from each professional sector of its remaining nationalities, designated by the regional councils, which may elect them themselves or through popular elections.
Ethiopia is a one party dominant state in that a coalition, the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF), dominates politics. Opposition parties are allowed. Elections were first held in Ethiopia under the provisions of the current constitution in June 1994 to elect the membership of local governments; general elections have since been held in 1995, 2000, 2005,2010 and 2015. In the May 2010 national parliamentary elections, the EPRDF and affiliated parties won 545 of 547 seats to remain in power for a fourth consecutive five-year term. In simultaneous elections for regional parliaments, the EPRDF and its affiliates won 1,903 of 1,904 seats.
ግንቦት 16/ቀን 2007 ዓ/ም የተካሄደው አገርአቀፍ ጠቅላላ ምርጫ ምን እንማራለን
Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front፡-{1} Tigrayan People’s Liberation Front {2} Oromo Peoples’ Democratic Organization {3} Amhara National Democratic Movement {4} Southern Ethiopian People’s Democratic Movement
Coalition for Unity and Democracy፡-{1} Ethiopian Democratic League {2} All Ethiopian Unity Party {3} United Ethiopian Democratic Party-Medhin Party {4} Rainbow Ethiopia: Movement for Democracy and Social Justice
United Ethiopian Democratic Forces፡-{1} Oromo National Congress {2} Ethiopian Social Democratic Federal Party {3} Southern Ethiopia People’s Democratic Coalition {4} All-Amhara People’s Organization {5} Ethiopian Democratic Unity Party
Other ethnic based political Parties in Ethiopia፡-{1} Somali People’s Democratic Party {2} Oromo Federalist Democratic Movement {3} Benishangul-Gumuz People’s Democratic Unity Front {4} Afar National Democratic Party {5} Gambela People’s Democratic Movement {6} Sheko and Mezenger People’s Democratic Unity Organization {7} Hareri National League {8} Argoba Nationality Democratic Organization
የወያኔን የሃያ አራት አመታት ታሪኬ ባጭሩን በመጨረሻው አገር አቀፍ ምርጫ ላይ ብቻ አተኩረን ቀሪውን ለታሪክ ተመራማሪዎች በመተው የሃገሪቱ የፖለቲካ ኢኮኖሚ ላይ የተደረጉ ዘርፈ ብዙ ጥናቶችን ላይ ብቻ በማተኮርና፣መረጃዎች በመጥቀስ ፁሁፉን እንቀጥላለን፡፡ የህወሃት የጦር አበጋዞችን ሥልጣን በደህንነትና በመከላከያ ሠራዊቱ ውስጥ የያዘውን ሥልጣን በመጨረሻው ምዕራፍ ከአያችሁ በኃላ የአገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ ተሳታፊ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገና ሳይወዳደሩ የተሸነፉ ለመሆናቸው የኒውክለር ፊዚክስ ሊቅ መሆን አያስፈልግም፡፡ ትንሽ እንካDን ‹ባትዋጋ እንካD በል እንገፍ እንገፍ፣ ያባትህ ጋሻ ትኃኑ ይርገፍ› እንደተባለው ተፎካካሪ ፓርቲዎች በህብረት እንደ አንድ ፓርቲ ተወዳድረው ቢሆን ማሸነፍ ባይችሉ የተወሰነ ወንበር ለማግኘት በቻሉ ነበር፡፡ በተናጥል ኢህአዴግን ለመግጠም ያደረጉት ውድድር በምንም መለኪያ የፖለቲካ ማህይምነት ነው፡፡ ያለ ብዙ ሃተታ ሠንጠረዦቹን በማየት ፍርዱን ለኢትዩጵያ ህዝብ ተትቶል፡፡
- ኢህአዴግ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት(501)ና ለክልል ምክር ቤቶች(1350) ያቀረቦቸው እጩዎች ብዛትና በመቶኛ፤ተፎካካሪ ፓርቲዎች ያቀረቡትን ያስተውሉ፡፡
ስልቻ፣ቀልቀሎ፣ቀልቀሎ፣ስልቻ
ግንቦት 16/ቀን 2007 ዓ/ም የተካሄደው አገርአቀፍ ጠቅላላ ምርጫ
- ኢህአዴግ ለህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት 501 እጩዎችን በማቅረብ 27.4 በመቶኛ፣መድረክ 270 እጩዎች በማቅረብ 15 በመቶኛ፣ሰማያዊ 139 እጩዎች በማቅረብ 8 በመቶኛ፣ኢትዩጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) 165 እጩዎች በማቅረብ 9 በመቶ ወዘተ እጩዎች አሳተፉ ማለት ለህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት ጠቅላላ ወንበር ብዛት 547 ተፎካካሪ ፓርቲዎች ተጣምረው ካልሆነ በተናጥል ተወዳዳሪ ዕጩዎች እንዳላቀረቡ እራሳቸው ያውቁታል፡፡ ሰለዚህ ለህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ለኢህአዴግ የምርጫ ፔስሜከር ወይም አbbጭ ከመሆን የዘለለ ምንም አልፈየዱም፡፡
- ኢህአዴግ ለክልል ምክር ቤት 1350 እጩዎችን በማቅረብ 39 በመቶኛ፣መድረክ 639 እጩዎች በማቅረብ 16 በመቶኛ፣ሰማያዊ 204 እጩዎች በማቅረብ 5 በመቶኛ፣ኢትዩጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ 172 እጩዎች በማቅረብ 4.3 በመቶ ወዘተ እጩዎች አሳተፉ ማለት ለክልል ምክር ቤት ጠቅላላ ወንበር ብዛት 1900 ተፎካካሪ ፓርቲዎች ተጣምረው ካልሆነ በተናጥል ተወዳዳሪ ዕጩዎች እንዳላቀረቡ እራሳቸው ያውቁታል፡፡ ሰለዚህ ለክልል ምክር ቤት ምርጫም ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለኢህአዴግ የምርጫ ፔስሜከር ወይም አbbጭ ከመሆን የዘለለ ምንም አልፈየዱም፡፡
- ቀሪውን ከሠንጠረዡ እያያችሁ ‹ሳይወዳደሩ የተሸነፉ› አሊያም ያገሬ ሰው ‹የተበላ ዕቁብ!!!› የሚለው ዐይነት ሆነብኝ!!! ቢያሸንፉ እንካD የትኛውን የወያኔ የጦር አበጋዝ ጀነራል መኮንኖችና የህዝብ ደህንነቶችን ሊያዙ ይሆን!!! በኢትዩጵያ ፖለቲካ የምርጫ ፔስሜከር ወይም አbbጭነት ይብቃ!!!
- The Ethiopian federal structure consists of nine regional states and two chartered city administrations. The administrative structure divides the nine regional states into 70 Zones and 550 Woreda (districts) with elected councils creating a four-tier level of government.
ግንቦት 16/ቀን 2007 ዓ/ም የተካሄደው አገርአቀፍ ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለህዝብ
ተወካዩች ምክር ቤትና ለክልል ምክር ቤቶች ያቀረቦቸው እጩዎች ብዛትና በመቶኛ
Number of candidates fielded by the contesting parties for the fifth nationwide election 2015
| የፖለቲካ ፓርቲዎች Political Partties | ለህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት For House of People’s Representatives | % | ለክልል ምክር ቤቶች For Regional Council | % |
| EPRDF | 501 | 27.4 | 1350 | 39.0 |
| FORUM(MEDREK) | 270 | 15.0 | 639 | 16.0 |
| SEMAYAWI(BLUE) | 139 | 8.0 | 204 | 5.0 |
| EDP | 165 | 9.0 | 172 | 4.3 |
| Coalition for Unity and Democracy | 108 | 6.0 | 119 | 3.0 |
| AEUO | 78 | 4.0 | 109 | 3.0 |
| UDJ | 92 | 5.0 | 95 | 2.4 |
| GPDM | 3 | 0.2 | 156 | 4.0 |
| ESPDP | 24 | 1.3 | 273 | 7.0 |
| APDP | 8 | 0.4 | 93 | 2.0 |
| BGPDP | 9 | 0.5 | 99 | 2.0 |
| RAEY | 42 | 2.3 | 62 | 1.5 |
| ANDP | 8 | 0.4 | 93 | 2.0 |
| OPDM | 8 | 0.4 | 85 | 1.6 |
| EDUM | 39 | 2.1 | 38 | 1.0 |
| EDU | 24 | 1.3 | 43 | 1.0 |
| EJDFF | 26 | 1.4 | 36 | 1.0 |
| SPDD | 15 | 0.8 | 43 | 1.0 |
| ONC | 23 | 1.3 | 31 | 1.0 |
| OSAP | 18 | 1.0 | 33 | 1.0 |
| AENM | 28 | 1.5 | 22 | 1.0 |
| EPDP | 16 | 1.0 | 20 | 1.0 |
| OPDO | 7 | 0.4 | 21 | 1.0 |
| Other Political Partties etc. | ||||
| Total Candidates | 1,828 | 3,991 |
Note:- 1,828 Candidates ran for House of People’s Representatives
3,991 Candidates ran for Regional Council
- 36.8 ሚሊዩን ህዝብ መራጭች ነበሩ፣ሩብ ሚሊዩን ምርጫ አስፈፃሚና የህዝብ ታዛቢዎች ነበሩ፣የምርጫ ጣቢያዎች ብዛት ተፎካካሪ ፓርቲዎች መወሰን ይኖርባቸዋል፡፡
ለህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት
- ለህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት ጠቅላላ ወንበር ብዛት 547 ሲሆን ለህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት የሚቀርቡ እጩዎች ብዛት 1,828 ነበር፡፡ በጊዜው ኢህአዴግ ለህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት የቀረበው እጩዎች ብዛት 501 ነበር፡፡ ኢህአዴግ አጋር ድርጅቶች ለህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት የቀረበው እጩዎች ብዛት እና ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት የቀረበው እጩዎች ብዛት አልተገለፀም ነበር፡፡
ለክልል ምክር ቤቶች
- ለክልል ምክር ቤቶች ጠቅላላ ወንበር ብዛት 1,900፣ ለክልል ምክር ቤቶች የሚቀርቡ እጩዎች ብዛት 3,991 ነበር፡፡ ኢህአዴግ ለክልል ምክር ቤቶች የሚቀርቡ እጩዎች ብዛት 1350 ነበር፡፡ ኢህአዴግ አጋር ድርጅቶች ለክልል ምክር ቤቶች የቀረበው እጩዎች ብዛትና ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለክልል ምክር ቤቶች የቀረበው እጩዎች ብዛት አልተገለፀም ነበር፡፡
ለህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት ካሉት 547 መቀመጫዎችና የህዝብ ብዛት
For House of People’s Representatives 547 seats
| ተ.ቁ | ክልል | የምርጫ ክልል /ወንበር ብዛት | የህዝብ ብዛት | የህዝብ ብዛት በመቶኛ | አሸናፊ የፖለቲካ ፓርቲ |
| 1 | ትግራይ | 38 | 4,929,999 | 5.8 | ሕወሓት/ኢሕአዴግ |
| 2 | አፋር | 8 | 1,602,995 | 1.9 | አብዴፓ |
| 3 | አማራ | 138 | 18,866,002 | 22.4 | ብአዴን/ኢሕአዴግ |
| 4 | ኦሮሚያ | 178 | 31,294,992 | 37.1 | ኦህዴድ/ኢሕአዴግ |
| 5 | ኢትዩጵያ ሶማሌ | 23 | 5,148,989 | 6.1 | ሶሕዴፓ |
| 6 | ቤንሻንጉል ጉምዝ | 9 | 982,004 | 1.2 | ቤጉሕዴፓ |
| 7 | ደቡብ ብ/ብ/ህዝቦች | 123 | 17,359,008 | 20.6 | ደኢሕዴን/ኢሕአዴግ |
| 8 | ጋምቤላ | 3 | 385,997 | 0.5 | ጋሕአዴን |
| 9 | ሐረሪ | 2 | 210,000 | 0.3 | ኦሕዴድ/ኢሕአዴግ/ሐብሊ |
| 10 | ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር | 2 | 387,000 | 0.5 | ኢሕአዴግ/ሶሕዴፓ |
| 11 | አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር | 23 | 3,041,002 | 3.6 | ኢሕአዴግ |
| ጠቅላላ ወንበር ብዛት | 547 | 84,320,987 | 100 |
ምንጭ፡- የኢትዩጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ለክልል ምክር ቤቶች ካሉት 1900 መቀመጫዎችና የህዝብ ብዛት
| ተ.ቁ | ክልል | የምርጫ ክልል/ወንበር ብዛት | የህዝብ ብዛት | የህዝብ ብዛት በመቶኛ | አሸናፊ የፖለቲካ ፓርቲ |
| 1 | ትግራይ | 152 | 4,929,999 | 5.8 | ሕወሓት/ኢሕአዴግ |
| 2 | አፋር | 96 | 1,602,995 | 1.9 | አብዴፓ |
| 3 | አማራ | 294 | 18,866,002 | 22.4 | ብአዴን/ኢሕአዴግ |
| 4 | ኦሮሚያ | 537 | 31,294,992 | 37.1 | ኦህዴድ/ኢሕአዴግ |
| 5 | ኢትዩጵያ ሶማሌ | 186 | 5,148,989 | 6.1 | ሶሕዴፓ |
| 6 | ቤንሻንጉል ጉምዝ | 99 | 982,004 | 1.2 | ቤጉሕዴፓ |
| 7 | ደቡብ ብ/ብ/ህዝቦች | 348 | 17,359,008 | 20.6 | ደኢሕዴን/ኢሕአዴግ |
| 8 | ጋምቤላ | 152 | 385,997 | 0.5 | ጋሕአዴን |
| 9 | ሐረሪ | 36 | 210,000 | 0.3 | ኦሕዴድ/ኢሕአዴግ/ሐብሊ |
| ጠቅላላ ወንበር ብዛት | 1900 |
ምንጭ፡- የኢትዩጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
- የትግራይና የሱማሌ ክልሎች የህዝብ ብዛት(ትግራይ 4,929,999፣ ሶማሌ 5,148,989 ሚሊዩን )ሆኖ እያለ ለህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት(ትግራይ 38፣ሱማሌ 23)ና ለክልል ምክር ቤቶች(ትግራይ 152፣ ሱማሌ 186)የወንበር ብዛት አላቸው፣ መስፈርቱና ሚዛኑ ምን የሆን!!!
- በአገሪቱ 78 ፖለቲካ ፓርቲዎች ህጋዊ እውቅና አግኝተው የመንቀሳቀስ መብት ተሰጥቶቸው 58 ፓርቲዎች በዘንድሮው አገራዊ ምርጫ ላይ በቅደመ ምርጫ ዝግጅት ሂደት ውስጥ መሳተፋቸውንም ተገልፆል፡፡
- In its recent history, Ethiopia is more fragmented now than ever on ethnic lines. On the National Election Board of Ethiopia website, there are 23 nation-wide parties, but there are 53 regional parties -TPLF created Kilil on ethnic based lines, that along with its constitution that guaranty secession-can lead to the breakdown of the country.
- በ2002 በተካሄደው አራተኛው አገራዊ ምርጫ ላይ 31 ሚሊዩን ዜጎች ካርድ መውሰድ የቻሉ ሲሆን፣ በዘንድሮው 5ኛው ምርጫ ከ36.8 ሚሊዩን በላይ መራጮች የምርጫ ካርድ መውሰዳቸውና 48 በመቶ ሴቶች መሆናቸው ታውቆል፡፡
- የጋምቤላ 385,997(0.5 በመቶ) የሃረሪ 210,000(0.3 በመቶ ) ክልላዊ መንግስቶች ከአምስት መቶ ሽህ ህዝብ በታች ሲኖራቸው በ1994 እኤአ የህዝብ ቆጠራ ዋቢ በማድረግ እንጂ አሁን ያለው ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን አትዘንጉ፡፡ በኢትዩጵያ ውስጥ፣ ከፍተኛ ህዝብ ቁጥር ያላቸው ጉራጌ 2,290,274 (4.3በመቶ)፣ ሲዳማ 1,842,314 (3.5በመቶ)፣ ወላይታ 1,269,216 (2.4በመቶ)፣ ሃዲያ 927,933 (1.7በመቶ)፣ ጋሞ 719,847 (1.4በመቶ)፣ ጌዲኦ 639,905 (1.2በመቶ)፣ ከፋ 599,188 (1.1በመቶ)፣ ከንባታ 499,825 (0.9በመቶ)፣ አገው 397,491 (0.7በመቶ)፣ ኩሎ 331,483 (0.6በመቶ)፣ ጎፋ 241,530 (0.5በመቶ)፣ እነዚህ ህዝቦች በአሁኑ ግዜ ቁጥራቸው የት እንደሚደርስ በመገመትና እንደሌሎች ህዝቦች ወደ ክልላዊ መንግስትነት የማደግ ፍትሃዊ ጥያቄ ብዙ ግዜ አንስተዋል ወደፊትም ማንሳታቸው የማይቀር ሲሆን ኢትዩጵያን የወያኔ የጦር አበጋዝ መንግስት አዙሪቱ በማያባራ ጦርነት ውስጥ በመክተትና የትግራዩ የጦር አበጋዝ መንግስት ሲያከትም የኦሮሞ፣ የአማራ፣ የደቡብ፣ወዘተ በዘር ላይ የተመሠረተ የዘመነ ጦር አበጋዞች መንግስት በቀጣይነት ሃገሪቱን ያሰጋታል፡፡
(ግንቦት 2007 ዓ/ም የተካሄደው አገርአቀፍ ጠቅላላ ምርጫ ሁኔታ የቀረበ ፁሁፍ ነበር!!!) ው

y
ዕለታዊ የዜና ዝማኔዎችን በኢሜይል ያግኙ… መረጃ ማግኘት መብተዎ ነው – ሳተናውNameEmail *Email *
MOST POPULAR

የፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳን መፀሐፍ”የአማራና ኦሮሞ እውነተኛው የዘር ምንጭ” የተባለውን የምትተቹና የምትቃወሙ…
January 6, 2017

የማይቀርበት ታላቅ አማራ አቀፍ ጉባኤ በኮሎምቦስ ኦህዮ ቅዳሜ ማርች 25 2017
March 14, 2017
