February 20, 2019 t

የአቶ ለማ ጽ/ቤት
” አቶ ለማን ማናገር አትችሉም”

የኦሮሞ ክልል መሬት አስተዳደር
“ቤታችሁ ከመፍረስ አይድንም። ልንተባበራችሁ አንችልም”

ዶ/ር አብይ ጽ/ቤት
“በኦሮሚያ ጉዳይ ጣልቃ አይገቡም”

ይሄን ጊዜ የኦሮሞ ቡድኖች ቢሆኑ ኖሮ የመጡት …..እናንተው አረፍተነገሩን ጨርሱት …

ቢቢሲ ከዘገበው የተወሰደ
—–

“ሌላኛዉ አስተያት ሰጭ እንደገለጹት ደግሞ “ሚስቴ ከወለደች ሦስት ቀኗ ነዉ። ከቤት ተባርራ ጎዳና ላይ ነች። ቤቱን ሲያፈርሱት እባካችሁ ሚስቴ ከወለደች ሦስት ቀኗ ነዉ ትንሽ ታገሱኝ ስል ‘ምን አገባኝ ከእኔ አልወለደች’ ሲል አንደኛው ምላሽ ሰጠኝ። እኔም የሚሰማ መንግሥት ይኖራል ብዬ ለአቤቱታ ትቻት መጣሁ። ሜዳ ላይ በተወጠረ ሸራ ውስጥ ነው ያለችው። ምን እንደሆነች አላውቅም” ሲሉ የተሰማቸውን ሐዘን ይገልፃሉ።

ትናንት ቤታቸዉ የፈረሰባቸዉ ግለሰቦች ዛሬ ጠዋት ተሰባስበዉ ወደ ኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ቢሮ ቢያመሩም እሳቸዉን ማናገር አትችሉም ተብለው ወደ ክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮ መላካቸውን ነግረውናል። ነገር ግን ከክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮም ያገኙት ምላሽ “ቤታችሁ ከመፍረስ አይድንም። ልንተባበራችሁ አንችልም” የሚል መሆኑን ገልጸውልናል።

አቤቱታ አቅራቢዎቹ በመቀጠል ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ቢያመሩም “ጉዳያችሁን እዛዉ ጨርሱ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ጉዳይ ጣልቃ አይገቡም” የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸዉ ለቢቢሲ ተናገረዋል።”

ኦሮሞ ያልሆነ በኦሮሞ ክልል ቤት ሰርቶ እንዲኖር አይፈለገም #ግርማካሳ

አቶ አዲሱ አረጋ የኦህዴድ ከፍተኛ አመራር፣ የዜጎችን ቤት የማፍረስ ሂደቱ እንደሚቀጥል፣ እንደው የበለጠ ተጠናክሮ እንዲሚቀጥል መግለጻቸው የኦ.ኤም.ኤኑ ግርማ ጉተማ ዘግቧል”

” Obboo Addisu Arega Kitessa from ODP’s secretariat office underscored today that the demolition of illegal houses will continue—even to be intensified” ሲል ነው የጻፈው።

አንደኛ – እነ አቶ አዲሱ ራሳቸው ሕግ ወጥ መስተዳድሮች ናቸው። ኢፍትሃዊ በሆነ ፣ በተጭበረበረ ፣ የመቶ በመቶ የዉሸት ምርጫ ነው መንግስት ስልጣን የያዙት። ሕግወጥ ሆነው ስለ ሕጋዊነት የማውራት የሞራል ብቃቱ የላቸውም።

ሁለተኛ – የሚያፈናቅሉት የአዲስ አበባ ዙሪያ ኦሮሞ ካልሆኑት ለማጽዳትና ኦሮሞዎች ከሌላ ቦታ አምጥቶ ለማስፈር እንጂ ሕግን ለማስክበር አይደለም። እነ አቶ አዲሱ ሕግ ወጥኘጥ ኦሮሞ አለመመሆን ነው። ሕገ ወጥ ቤቶች የሚሉት ኦሮሞ ያልሆኑ ወይንም ኦሮሞ ሆነው የነርሱ አመላከካት የማይጋሩ ዜጎችን ቤት ነው። ጭንቀታቸው በአዲስ አበባና በአዲስ አበባ ዙሪያ እነርሱ ኦሮሞ የሚሉትን በቁጥር እንዴት የበላይ እናድርገው የሚለው ነው።

ሶስተኛ – እየተፈናቀሉ ያሉ ወገኖች የቤት ባለቤትነትስ ሰነድ ያላቸው፣ ማስረጃ ያላቸው፣ የመብራትና የዉሃ አግልግሎት የቀረበላቸው፣ ለነዚህ አጋለግሎቶች ክፍያ ሲከፍሉ የነበሩ ናቸው።

አራተኛ – ቤቶቹ ሕግ ወጥ ናቸው ቢባልም እንኳን፣ ሕጻናት፣ አረጋዉያን፣ እናቶች ..አሉ። ሕግ ወጥ ነው ተብሎ፣ ሌላ ማረፊያ እንደ መንግስት ሳይዘጋጅላቸው፣ ሜዳ ላይ መበተን የለየለት አረመኔነት ነው።

አቶ አዲሱ ይሄንን ድርጒት ማውግዘ ሲገባው ድርጊቱን ደግፎ መናገሩ ከማሳዘን በላይ የሚያበሳጭ ነው። ከአንድ የመንግስት ባላስልጣን የሚጠበቅ ሳይሆን የለየለት ዉንብድናና መንግስታዊ ሽብርተኘንት ነው።475