March 7, 2019

ቁጥር 2

ሰላም የህይዎት ዋስትና ነዉ

ሰላምና መረጋጋት የሌለበት መንግሥት ምንጊዜም ቢሆን ለዜጎች የህይዎት ዋስትና አይሰጥም ። በአገራችን ኢትዮጵያ እየታየ ያለው ለውጥ ገና አንድ አመት ያልሞላው ስለሆነ  መንግስት ለሃያ ሰባት ዓመታት ሲጎነጎን የኖረውን ሴራ በአጭር ጊዜ ውስጥ መፍትሔ ይሰጣል የሚል እምነት ባይኖረንም በአጭር ጊዜ ውስጥ ሊተገበሩ የሚገባቸውን የዜጎችን ደህንነት ማስከበር በተመለከተ እየታየ ያለው ዳተኝነትና ለውጡ ይነካናል ብለው በማሰብ እየሞተ ያለው ስርአት እንዲያንሰራራ የሚጥሩ ሀይሎችን በፍጥነት ማጽዳት ባለመቻሉ በብዙ አከባቢዎች ጎሳን ምክንያት እያደርጉ የሚነሱ ግጭቶች የበርካታ ሰዎችን ህይዎት ቀጥፏዋል፤ አካል አጉድለዋል፤ ብዙ ዜጎች ሀብት ንብረት አፍርተው ከኖሩበት ቀየ አፈናቅሏል።

በጎሳ ግጭት ምክንያት ጎዳት ከደረሰባቸው አካባቢዎች አንዱ ጎንደር ነዉ ። በተለይም በስሜን ምዕራብ አካባቢ ቅማንትና አማራ በሚል ሰበብ የተለያዩ ኃይሎች በቀጥታም ሆነ ከጀርባ በመሆን በቆሰቆሱት ግጭት ከሁሉም ወገን ቁጥሩ በውል ያልታወቀ የብዙ ሰው ህይወት ተቀጥፏል፤ ቤቶችና የንግድ ቦታዎች ተቃጥለዋል፤ የእህል ክምሮች ሳይቀር በመቃጠላቸው አንድ አመት ሙሉ የተለፋበት ምርት እንዳለ ወድሟል። በዚህ ሰበብ ስዎች ከመተማ፤ ከቋራ፤ ከጭልጋና አካባቢው ባሉ ከተሞችና የገጥር ቦታዎች ዘርን መሰረት አድርጎ ከሁለቱም ህዝቦች በኩል  ከእኔ አከባቢ ውጣ በሚል በብዙ ሺህ የሚቆጠር ሕዝብ ተፈናቅሎ፤ በተለያዩ የመጠለያ ቦታዎች ታጎረው በርሃብና በተላላፊ በሽታ እየተሰቃዮ ይገኛሉ። በተመሳሳይ ሁኔታ በላይ አርማጭሆ፤ በታች አርማጭሆ፤ በምዕራብ አርማጭሆና በጠገዴ እስከ 14 ሺህ የሚደርስ ሕዝብ ከመንግሥት መስሪያ ቤት፤ ከንግድ ቦታ እና ከርሻ ቦታዎች ተፈናቅለው ትክል ድንጋይ ፤ ሳንጃ፤ ጎንደርና ወለቃ በሰፈራ ጣቢያ ውስጥ በበሽታና በርሃብ በመሰቃዬት ላይ ናቸው። ትክል ድንጋይ ላይ በጊዜያዊ መጠለያ የታጎረው ሕዝብ እስከ 10 ሺህ ሲሆን፤ ወለቃ ደግሞ 4 ሺህ  እንደሚደርስ ከአካባቢው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። እንዲሁም እንደ ትክል ደንጋዩና ወለቃው ሁሉ ፤ በአይንባ 9 ሺህ፤ በጫንድባ ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ብዙ ሕዝብ በጊዜያዊ መጠሊያ በርሃብና በበሽታ እየተሰቃየ ይገኛል።  የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኮሚኒኪሽን ጽ/ቤት በማዕክላዊና በምዕራብ ጎንደር 100 ሺህ ሕዝብ መፈናቀሉንና 6 ሺህ ቤቶች መቃጠላቸውን ሲገልጽ፤ የሞቱትንና የአካል ጉዳተኞችን አላሳወቀም።

ጎንደር ከተማም ቢሆን በሥጋት ቀጠና ውስጥ ናት ፤ በርካታ ወጣቶች ክላሽ ጠመንጃ ታጥቀው በጠራራ ጸሐይ በከተማ ውስጥ ላይ ታች ላይ ሲሉ መሰንበታቸው ጸሐይ የሞቀው፤ መንግስትም ያወቀው ጉዳይ ነው። መሣሪያውን መቸና በምን ሆኔታ እንደሚጠቀም ስልጠና ያልወሰደ ወጣት አንድ ግርግር ቢፈጠር በሰላማዊ ስዎች ላይ ምን ያህል መጥፎ ጉዳት ሊያደርስ እንደሚችል መገመት አያቅትም

ለደረሰው ክቡር የሰዎች ህይዎት መጥፋትና ንብረት ውድመት በእኛ እምነት ተጠያቂ ናቸው የምንላቸውን አካላት እንደሚከተለው ለመግለጽ እንፈልጋለን ፤

  1. 1. መንግስትን በተመለከተ
  1. 2. “የቅማንት የማንነትና የራስ አስተዳደር ጥያቄ አቅራቢ ኮሚቴ” ነኝ ባዩን ቡድን በተመለከተ

ሕዝባችን ሰላም ወዳድ ነው። አርሶና ነግዶ መኖር እንጅ እርስ በርስ መሻኮት የሚፈልግ ህዝብ አይደለም። ሳይፈልግና ሁኔታውን በቅጡ ሳይረዳ በተንኳሽ ኃይሎች ተገፍቶ ጊዚያዊ ግጭት ውስጥ ገብቷል። ከዚህ በመነሳት በሰሜን አሜረካ የምንገኝ የቅማንት ተወላጆች የመከላከያ ሰራዊት በአካባቢው ገብቶ እያካሄደ ያለውን የሰላም ማስከበር ሥራ እያደነቅን አሁን ለተከሰተው ችግር በእኛ በኩል ተጨማሪ መፍትሔ ይሆናል የምንላቸውን ሀሳቦች ከዚህ እንደሚከተለው እናቀርባለን።

መንግሥት፤

በመጨረሻም የጎንደር ጌጡ አንድነቱ፤ የጎንደር አንድነት የሚከበረው በእኛ በአማራና ቅማንት ልጆች አንድነት ነው። በመከፋፈላችን የሚደሰትና ጎንደር በነደደው እሳት የሚሞቅ ጠላት ብቻ ነው። በዚህ አደጋ ህይዎታቸውን ላጡ ፈጣሪ ነብሳቸውን በሰላምና በገነት ያስርፍልን፤ ሐዘን ለደረሰባችሁ ሐዘኑ የሁላችን ነውና መጽናናቱን ይስጠን።

ኢትዮጵያ ለዘላለም በአንድነቷ ጸንታ ትኑር!!

ጎንደር በሴረኞችና በዘረኞች አትፈታም!!!

ሰላም ለሕዝባችን!!!

አገራችን እግዚአብሔር ይባርክልን!!!

የካቲት ፳፫ ፪ሺ፲፩ ዓ.ም

ግልባጩ፤

ኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት

ለአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት

ለአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት

Ethiopian Broadcasting Corporation (EBC)

ለFana Boadcasting Corporate S.C (ፋና ሬድዮ)

ለWalta Media and Communication SC (ለዋልታ ቲቪ ዜና አገልግሎት)

ለEthiopian Television (ለኢቲቪ)

ለኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥንና ሬድዮ (Ethiopian Satellite Television &  Radio (ESAT)))