የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዑክ ማይክ ሐመር መግለጫ

September 14, 2024 – DW Amharic  ሰሞኑን ወደ ኢትዮጵያ የመጡት የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልእክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር የሰሞኑ ጉዟቸው አላማ ኢትዮጵያ ውስጥ በየክልሎች የሚካሄደውን ግጭት ለማስቆም ውይይት ማድረግ እና በትግራይ ክልል የጠመንጃ ላንቃ መዘጋቱን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑን ገልፀዋል።… … ሙሉውን ለማየት ወይም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

ለምን 5,4 % ብቻ ተፈታኞች የ12ኛ ክፍል ፈተናን አለፉ?

September 14, 2024 – DW Amharic  የ2016ዓም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 684,205 ተማሪዎች መካከል ያለፉት 36,409 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ቁጥሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ አሁንም አነስተኛ የሚባል ነው። ችግሩ የቱ ጋር ነው ያለው? ለዚህስ ምክንያት እና መፍትሔው ምን ይሆን?… … ሙሉውን ለማየት ወይም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

ጀርመን 250 ሺህ ኬንያውያን ሠራተኞችን ልትቀጥር ነው

ከ 6 ሰአት በፊት ጀርመን ለ250 ሺህ ኬንያውያን ሠራተኞች በሯን ልትከፍት መሆኑ ተሰማ። የኬንያ እና የጀርመን መንግሥት ባደረጉት የሥራ ስምምነት መሰረት በከፊል እንዲሁም ሙሉ በሙሉ የሰለጠኑ 250 ሺህ ኬንያውያን ሠራተኞች ወደ ጀርመን ይሻገራሉ ተብሏል። ኬንያውያን ሠራተኞችን በአውሮፓ ትልቁ ኢኮኖሚ ባለቤት በሆነችው ጀርመን ለመቅጠር በሚል አገሪቱ ያላትን የስደተኞች ሕግ ለማላላት ተስማማታለች። ኬንያ በአገሯ ውስጥ ለወጣት ባለሙያዎች […]

የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛው በህወሓት መካከል የተፈጠረው አለመግባባት በንግግር እንዲፈታ ጥሪ አቀረቡ

ከ 4 ሰአት በፊት በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ሲያደርጉ የቆዩት አምባሳደር ማይክ ሐመር በህወሓት መካከል የተፈጠረው አለመግባባት በንግግር እንዲፈታ ጥሪ አቅርበዋል። ልዩ መልዕክተኛው አምባሳደር ማይክ ሐመር በትናንትናው ዕለት በአሜሪካ ኤምባሲ ቅጥር ግቢ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የፕሪቶሪያውን ስምምነት በተሟላ መልኩ መተግበር እንደሚያስፈልግ እና ለዚህም ሁለቱም አካላት ቁርጠኛ መሆናቸውን እንዳረጋገጡላቸው ተናግረዋል። በአፍሪካ ቀንድ የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ መልዕክተኛው የፕሪቶሪያ […]

የካቶሊኩ ጳጳስ አሜሪካውያን ከትራምፕ እና ካማላ “የተሻለውን ክፉ” እንዲመርጡ ጠየቁ

ከ 3 ሰአት በፊት የካቶሊኩ ጳጳስ ፍራንሲስ ሁለቱም ለአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እጩ ሆነው የቀረቡት “ከሕይወት በተቃራኒ የቆሙ” መሆናቸውን ገልጸው፣መራጮች ድምጻቸውን በሕዳር ወር ሲሰጡ “የተሻለውን ክፉ” እንዲመርጡ ጥሪ አቀረቡ። የሮማው ጳጳስ ስደተኞችን አለመቀበል፣ትራምፕን ማለታቸው ነው፤ “ከባድ” ሀጥያት ሲሆን ካማላ ሐሪስ የሚደግፉትን ጽንስን ማቋረጥ ደግሞ “የነፍስ ማጥፋት” ሲሉ ኮንነውታል። ጳጳሱ በደቡብ ምዕራብ እስያ እያደረጉ የነበረውን ጉብኝት ሲያጠናቅቁ […]

በኮንጎው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ የአሜሪካ እና የእንግሊዝ ዜጎችን ጨምሮ 37 ግለሰቦች ሞት ተፈረደባቸው

ከ 4 ሰአት በፊት የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን ፕሬዚደንት ከሥልጣን ለማስወገድ መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በመፈፀም ሦስት አሜሪካውያን፣ እንግሊዛዊ፣ ቤልጂየማዊ እና ካናዳዊን ጨምሮ 37 ግለሰቦች የሞት ፍርድ ተበየነባቸው። ግለሰቦቹ ግንቦት ወር ላይ በፕሬዚደንቱ ቤተ መንግሥት እና የፕሬዚደንት ፊሊክስ ታሺኬዲ አጋር መኖሪያ ቤት ላይ ጥቃት እንዲፈፀም በመምራት ነበር ክስ የቀረበባቸው። መፈንቅለ መንግሥቱ እንዲፈፀም በመምራት የተጠረጠረው ትውልደ ኮንጎያዊው የሆነው […]

የሞባይል ስልካችን የመሬት መንቀጥቀጥን ለመለየትና ማስጠንቀቂያ ለማግኘት እንደሚያስችል ያውቃሉ?

ከ 7 ሰአት በፊት የሰው ልጅ የመጀመሪያውን የሞባይል ስልክ ጥሪ ካደረገ 50 ዓመታት በኋላ በኪሳችን የምንይዘው ቴክኖሎጂ የመሬት መንቀጥቀጥን ለመለየት እየረዳ ይገኛል። እአአ በ2022 በካሊፎርኒያ ቤይ ኤሪያ በርዕደ መሬት መለኪያ (ሬክተር እስኬል) 5.1 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር። እንደ ዕድል ሆኖ ኃይለኛ ንዝረት እንጂ ከባድ መንቀጥቀጥ አልነበረም። ንዝረቱ የተሰማቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ወደ ዩናይትድ ስቴትስ የጂኦሎጂካል […]