የዩኒቨርስቲ የመውጪያ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች ዕጣ ፈንታ ምን ይሆናል?
ከ 9 ሰአት በፊት በኢትዮጵያ በዩኒቨርስቲዎች የመውጪያ ፈተና ሰኔ 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ ከተሰጠ በኋላ ለመውጫ ፈተናው ከተቀመጡት 61ሺ 54 ተማሪዎች 40.65 በመቶ የማለፊያውን ነጥብ ማስመዝገባቸውን ሚኒስቴሩ ይፋ አድርጓል። 62.37 በመቶ የመንግሥት ተቋማትና 17. 2 በመቶ የግል ተቋማት ተማሪዎች የማለፊያውን 50 በመቶና ከዛም በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውም በወቅቱ ተገልጾ ነበር። ቢቢሲ በጉዳዮ ላይ ያነጋገራቸው የሚኒስቴሩ ከፍተኛ ኃላፊ […]
በጋና ከሚኒስትሯ መኖርያ ቤት ከ1 ሚሊዮን ዶላር በላይ በመስረቅ የተጠረጠሩት የቤት ሠራተኞች
ከ 4 ሰአት በፊት የጋና ውሃ ሀብት እና ፍሳሽ ሚኒስቴር፣ ሲሲሊያ ዳፓ፣ ሁለት የቤት ሠራተኞች ከአንድ ሚሊዮን ዶላር በላይ በመስረቅ ተጠርጥረው ፍርድ ቤት ቀረቡ። የቤት ሠራተኞቹ በርካታ ሚሊየን የጋና ቼዲ የተገመተውን ገንዘብ (ከ1 ሚሊዮን ዶላር በላይ) የሰረቁት አክራ ከሚገኘው የሚኒስቴሯ መኖርያ ቤት ነው ተብሏል። የጋና አገር ውስጥ መገናኛ ብዙኀን እድሜያቸው 18 እና 30 መሆናቸውን የተነገረላቸው […]
ዶናልድ ትራምፕ የሚቀጥለው ዓመት ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ተቀጠረ
ከ 7 ሰአት በፊት የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሰነድን በአግባቡ ባለመያዝ በሚቀጥለው ዓመት ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ተወሰነ። ፍርድ ቤቱ ጉዳያቸው በሚቀጥለው ዓመት ግንቦት ወር እንዲታይ ወስኗል። እርሳቸው ግን የፍርድ ቤት ጉዳያቸው ከ2024 ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በኋላ እንዲደረግ ሃሳብ አቅርበዋል። ዓቃቤ ሕግ በበኩሉ ከምርጫ በፊት መታየት እንዳለበት ተከራክሯል። የ77 ዓመቱ ትራምፕ የመንግሥት ወሳኝ መረጃዎችን ፍሎሪዳ በሚገኘው […]
ወንድ ነው የተባለው ጎሬላ ልጅ ወልዶ የመካነ አራዊቱን ባልደረቦች አስገረመ
ከ 8 ሰአት በፊት ለአራት ዓመት ያህል በኦሃዮ መካነ አራዊት ውስጥ ወንድ መሆኑ ይታወቅ የነበረ ጎሬላ ልጅ ወልዶ ሠራተኞቹን አስገርሟል። ኮለምበስ በተሰኘ መካነ አራዊት እኤአ ከ2019 ጀምሮ ትኖር የነበረችው ሳሊ፣ ሐሙስ እለት ልጇን ታቅፋ ተገኝታለች። የመካነ አራዊቱ ሰራተኞች የጎሬላዋ ልጅ “በመልካም ጤንነት ላይ” እነደምትገኝ በብሎጋቸው ላይ አስፍረዋል። ይህ ወንድ ነው ተብሎ የታመነችው ጎሬላ፣ ስሟ ሳሊ […]
በጠለምትና አካባቢው በትግርኛ ቋንቋ የሚጠሩ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ስያሜ ወደ አማርኛ ሊቀየር መሆኑ ተሰማ
July 22, 2023 በጠለምትና አካባቢው በትግርኛ ቋንቋ የሚጠሩ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ስያሜ ወደ አማርኛ ሊቀየር መሆኑ ተሰማ (አዲስ ማለዳ) በአማራ እና ትግራይ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች የሚገኙና በትግርኛ ቋንቋ የሚጠሩ ወረዳዎች እና ቀበሌዎች ስያሜ ወደ አማርኛ ቋንቋ ሊቀየር መሆኑን አዲስ ማለዳ ከጠለምት አማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ ሰምታለች። ኮሚቴው በጠለምትና አካባቢው የሚገኙና በትግርኛ ቋንቋ ስያሜ ያላቸው ኹሉም ወረዳዎች፤ […]
ዳይሬክተር ጀኔራል ተስፋሁን ጎበዛይ ከሃላፊነት መልቀቃቸውን አሳወቁ
July 22, 2023 – Konjit Sitotaw የኢትዮጵያ የስደተኞችና ስደት ተመላሾች አገልግሎት ዳይሬክተር ጀኔራል ተስፋሁን ጎበዛይ ከዛሬው ዕለት ጀምሮ ከሃላፊነት መልቀቃቸውን በትዊተር ገጻቸው ባሠራጩት የስንብት ደብዳቤ አስታውቀዋል።
የትረምፕ ክሥ የሚሰማበት ቀጠሮ ተሰጠ
VOA Amharic ጁላይ 21, 2023 በዩናይትድ ስቴትስ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ላይ፣ የምስጢራዊ ሰነዶች አያያዝን በተመለከተ፣ የቀረበባቸውን ክሥ ለመስማት፣ ፍርድ ቤት ቀጠሮ ሰጠ። የክሡ ሒደት፣ ከዘጠኝ ወራት በኋላ፣ እ.አ.አ ግንቦት 20 ቀን 2024፣ ፍሎሪዳ በሚገኘው የፌዴራል ፍርድ ቤት እንዲታይ፣ ዳኛ አይሊን ካነን ቀነ ቀጠሮ ሰጥተዋል። ቀጠሮው፣ በመጪው ዓመት ኅዳር ወር ከሚደረገው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ስድስት ወር […]
በኬንያ አንዳንድ ቦታዎች ግጭት ቢስተዋልም ተቃውሞው ግን እየቀነሰ ነው
VOA Amharic ጁላይ 21, 2023 በኬንያ፣ በትላንትናው ዕለት በአብዛኛው በተቃዋሚው ፓርቲ በተጠራው ሰልፍ ላይ፣ የአገሪቱ ዜጎች በብዛት ባይሳተፉም፣ በአንዳንድ ቦታዎች ግን፣ ድንጋይ በሚወረውሩ ተቃዋሚ ሰልፈኞች እና በፖሊስ መካከል ግጭት ተፈጥሮ ነበር። ኪብራ በተሰኘው፣ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙና የተቃዋሚው ራይላ ኦዲንጋ ፓርቲ ደጋፊዎች በብዛት በሚኖሩበት አካባቢ፣ ፖሊስ አስቃሽ ጢስ እና ጥይት መተኮሱን፣ የኤኤፍፒ ዜና ወኪል ተመልክቷል። ተቃዋሚው ራይላ ኦዲንጋ፣ በሳምንት ውስጥ ለሦስት ቀናት የሚቆይ ተቃውሞ እንዲደረግ ጥሪ ቢያደርጉም፣ በረቡዕ ተቃውሞ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን፣ የአምንስቲ ኢንተርናሽናል ኬንያ ቢሮ አስታውቋል። ካለፈው መጋቢት ወዲህ፣ 20 ሰዎች ከተቃውሞ ጋራ በተያያዘ እንደሞቱ መንግሥት ሲያስታውቅ፣ ፕሬዚዳንቱ ዊሊያም ሩቶ፣ ትላንት ኀሙስ ሰልፉ እንዲቆም በድጋሚ ጥሪ ሲያደርጉ፣ “የተቃውሞ ሰልፎች ለኬንያ ችግሮች መፍትሔ አያመጡም፤” ብለዋል። የኑሮ ውድነትንና የታክስ ማሻቀብን በመቃወም፣ ኦዲንጋ፣ ካለፈው ሚያዝያ ወር ጀምሮ፣ ሕዝቡ ለተቃውሞ እንዲወጣ ጥሪ አድርገው ነበር።
የኦሮሞ ዳያስፖራ ማኅበረሰብ ተወካዮች እና አምባሳደር ማይክ ሐመር ተወያዩ
ጁላይ 21, 2023 የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር፣ በዩናይትድ ስቴትስ ከትውልደ ኢትዮጵያውያን የኦሮሞ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋራ እንደተወያዩ፣ የኦሮሞ ቅርስ አመራር እና ተሟጋች ማኅበር አስታወቀ። የኦሮሞ ዳያስፖራ ተወካዮቹ፣ የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት፣ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ጥሎት የነበረውን የርዳታ ማዕቀብ መልሶ ማንሣቱ እንዳሳዘናቸው፣ ለአምባሳደር ማይክ እንደተናገሩ፣ መግለጫው አመልክቷል። ምክንያት ያደረጉትም፣ በኢትዮጵያ፣ አሁንም አለ ያሉትን የሰብአዊ […]
ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን በሱዳን አገልግሎቱ ቀጣይነት ላይ አደጋ የጋረጠ ጥቃት እንደገጠመው አስታወቀ
ጁላይ 21, 2023 በትላንትናው ዕለት፣ የድንበር የለሽ ሐኪሞች ቡድን(MSF) ሠራተኞች የኾኑ 18 የቡድኑ አባላት፣ የሕክምና ቁሳቁሶችን፣ በደቡባዊ ካርቱም ወደሚገኘው የቱርክ ሆስፒታል ለማድረስ በሚያጓጉዙበት ወቅት፣ በቡድን በተደራጁ ታጣቂዎች፣ ዐመፅ የተቀላቀለበት ጥቃት ደርሶባቸዋል፤ ሲል፣ ተቋሙ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ታጣቂዎቹ ጥቃቱን የፈጸሙት፣ ኤም.ኤስ.ኤፍ በሥፍራው በመገኘቱ ላይ ከተደረገ ክርክር በኋላ፣ ሠራተኞቹ አካላዊ ግርፊያ እና ድብደባ ተፈጽሞባቸዋል፤ ብሏል፡፡ በተጨማሪም፣ […]