ግንቦት 20 የወለደው የመለያየት አደጋ!

የግንቦት ሃያ 23ኛ ዓመት በተለያዩ ዝግጅቶች በመከበር ላይ ነው፡፡ ኩነቱን ምክንያት በማድረግ የመንግሥት መገናኛ ብዙኃንና የድርጅቱ (ኢሕአዴግ) አመራሮች ግንቦት ሃያ ለሀገራችን “አስገኝቷቸዋል” የሚሏቸውን ትሩፋቶች እየዘረዘሩ የተለያዩ ዘገባዎችን በማቅረብ ላይ ናቸው፡፡ የዕንቁ ባልደረቦች በበኩላቸው ግንቦት ሃያ “መጣብን ወይስ መጣልን?” ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡ ግንቦት ሃያን በሚመለከት፣ የመንግሥት መገናኛ ብዙኃንና የኢሕአዴግ አመራሮች የሚያስቀምጧቸው የተለመዱ ተረኮች አሉ፡፡ “ሀገራችን የዛሬ ሃያ ሶስት ዓመት መስቀለኛ መንገድ ላይ ነበረች፤ የብተና አደጋ ተጋርጦባት ነበር፤ ከዚህ ሁሉ አደጋ የታደጋት ኢሕአዴግ የሚመራው መንግሥት ነው” ወዘተ ይባላል፡፡ የኢሕአዴግ መሪዎች እንደሚሉት አሁንም ቢሆን ሀገራችንን ከአደጋ ሊታደጋት የሚችለው የኢሕአዴግ መስመር ብቻ ነው፡፡ ሕዝቡም ወይ የኢሕአዴግን ‹‹ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ›› መስመር ወይ ደግሞ የተቃዋሚዎችን ‹‹ፀረ-ልማትና ፀረ-ዴሞክራሲያዊ›› መንገድ ሊመርጥ እንደሚችል፤ የተቃዋሚዎችን መስመር መከተል ግን ሀገሪቱን ወደ ጥፋት እንደሚወስዳት አበክረው ሲገልጹ ቆይተዋል፡፡ ለመሆኑ በአገዛዙ በኩል ሲነገሩ የቆዩትና በመነገር ላይ ያሉት ነጥቦች ምን ያህል ውሃ የሚቋጥሩ ናቸው? የተወሰኑትን እንመርምራቸው፡፡ የኢኮኖሚው ሁኔታ አገዛዙ በተለያዩ ሰነዶቹ እንደሚገልጸው ከተሃድሶው በፊት ባሉት 10 ዓመታት ውስጥ ያለምንም የጠራ ርዕዮተ-ዓለምና ስትራቴጂ ሲንገዳገድ ቆይቶ በድርጅቱ በተለይ በሕወሓት ውስጥ የተከሰተው መከፋፈል (የተወሰኑትን አመራሮች ከአባልነት በማስወገድና የተወሰኑትን በማሰር) ከተወገደ በኋላ በተሃድሶው ወቅት የተለያዩ የልማት ስትራቴጂዎችን ቀርፆ መንቀሳቀስ በመጀመሩ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ማስመዝገብ ችሏል፡፡ በተለይ ላለፉት ስምንት ዓመታት በተከታታይ ሲመዘገብ የቆየው ዕድገት የስትራቴጂውን ትክክለኛነት ያረጋገጠ እንደሆነ በሰፊው ይነገራል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ መንግሥት የሚለውን ያህል ባይሆንም ኢኮኖሚዊ ዕድገት መኖሩን ብዙ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች መስክረዋል፡ ፡ በቅርቡ ሙዲስና ፊችና ስታንደርድ ኤንድ ፑር የተባሉት የተባሉት ታዋቂ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችም የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሁኔታና ብድር የማግኘት ዕድሏን ገምግመው ሁለቱም ድርጅቶች ቢ አንድ (B1) ሰጥተዋታል፡፡ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት መኖሩን ላለፉት አሥርት ዓመታት የተሠሩትን መንገዶችና፣ ግድቦችና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን እንዲሁም በግሉ ዘርፍ የሚሠሩ ፕሮጀክቶችንና ሌሎች እንቅስቃሴዎችን በመመልከት ማንም ሊመሰክርለት ይችላል፡፡ መጠኑ ቢያከራክርም ዕድገት ስለመኖሩ የ ብዙዎች ይስማማሉ፡፡ ጥያቄ የሚነሳው ዕድገቱ ምን ዓይነት ዕድገት ነው? ከዕድገቱ ተጠቃሚ የሆኑት ወገኖች እነማን ናቸው? ወዘተ በሚሉት ነጥቦች ላይ ነው፡፡ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅትና ዓለም ባንክ በተደጋጋሚ እንደገለጹት የኢትዮጵያ መንግሥት በኢኮኖሚው ውስጥ ያለው ተሳትፎ እጅግ የተጋነነና አሳሳቢ ነው፡፡ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የኢትዮጵያ መንግሥት በኢኮኖሚው ውስጥ ያለው ተሳትፎ እጅግ የተጋነነ (በዓለም በኢኮኖሚ ውስጥ ከፍተኛ ተሳትፎ ከሚያደርጉ ሶስት መንግሥታት አንዱ ነው) በመሆኑ የግሉን ዘርፍ ዕድገት እያቀጨጨው ነው፤ ስለዚህም ተሳትፎውን መቀነስ እንዳለበት ሲያሳስብ ቆይቷል፡፡ ስለዚህ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ቢኖርም ዕድገቱ በግሉ ሴክተር እንቅስቃሴ የተመዘገበ አለመሆኑ ደግሞ ግልጽ ነው፡ ፡ ይህ አንዱ ችግር ነው፡፡ ሌላም ነጥብ አለ፡፡ የግል ዘርፍ የሚባለው አካልም በብዙ መልኩ ሊታይ የሚገባው ነው፡፡ በአንድ በኩል አቶ ክቡር ገና በአንድ ጽሑፋቸው እንዳሉት ከመንግሥትና ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር አብረው በመሥራት በጣም በአጭር ጊዜ የከበሩ ‹‹ፓራሹት ነጋዴዎች›› አሉ፡፡ እነኝህ አካላት በጥቂት ዓመታት ውስጥ በሚያስገርም ፍጥነት የብዙ መቶ ሚሊዬን ባለንብረቶች የሆኑ ናቸው፡፡ ከዕድገቱ በከፍተኛ ደረጃ ተጠቃሚ የሆኑት እነኝህ አካላት ናቸው፡፡ በኢንዶውመንት ስም የሚንቀሳቀሱት ግዙፍ የፓርቲ ድርጅቶችም በግሉ ዘርፍ ሥር የሚጠቃለሉ ናቸው – በመንግሥትም በዓለም አቀፍ ድርጅቶችም፡፡ ይሁን እንጂ እነኝህን ግዙፍ ድርጅቶች በኃላፊነት የሚያንቀሳቅሷቸው የኢሕአዴግ መሪዎች መሆናቸው ደግሞ የታወቀ ነው፡፡ የአገዛዙ መሪዎች የሚመሯቸው ድርጅቶች ከሌላው የግል ዘርፍ አኩል ይንቀሳቀሳሉ፤ የበለጠ እንክብካቤ አይደረግላቸውም ማለት በጭራሽ አይቻልም፡፡ እንደሚታየውም በግል ጥረቱ የሚፍጨረጨረው ነጋዴ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከገበያ ውጪ ሲሆን እነኝህ ድርጅቶች በአንጸሩ እየገነኑ በመሄድ ላይ ናቸው፡፡ አቶ ስብሃት ነጋ በአንድ ወቅት ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ እንደገለጹት ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ የኤፈርትን ያህል ትልቅ ሀብት የሚያንቀሳቅስ ድርጅት የለም፡፡ ድርጅቱ ይህን ያህል ግዙፍ ሀብት ያፈራው ባለፉት ሃያ ሶስት ዓመታት ውስጥ ነው፡፡ እንዴት እንደዚህ ሊያድግ ቻለ? በኢኮኖሚው ውስጥ ያለ ያልተፈታ ጥያቄ ነው፡፡ ኢኮኖሚያው ዕድገቱ በጥረቱ የሚንቀሳቀሰው የግል ባለሀበት የተመዘገበ አለመሆኑ ዋናው የሀገሪቱ ራስ ምታት ነው፡፡ ዕድገቱ የተገኘው በአብዛኛው በመንግሥት እንቅስቃሴ ነው፡፡ መንግሥት ለተለያዩ የልማት ተግባራት የሚያወጣው አብዛኛው ገንዘብም በብድር የተገኘ መሆኑም ይታወቃል፡፡ ከዕድገቱ የሚጠቀሙት አካላት ደግሞ የመንግሥት አካላትና ከእነሱ ጋር አብረው የሚሠሩት ‹‹የፓራሹት ነጋዴዎች›› ናቸው፡ ፡ ሌላው ሁሉ የበይ ተመልካች ነው፡፡ በዚህ ዓይነት ግልጽነትና ተጠያቂነት በሌለበት የቢዝነስ ከባቢ ውስጥ ሕገ-ወጦች ሲያድጉ በጥረታቸው ለማደግ የሚንቀሳቀሱት ከገበያ ውጪ ይሆናሉ፡፡ ብሔራዊ ከበርቴ መፍጠር አይቻልም፤ አልተፈጠረም፡፡ ‹‹ግብርና መር የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂው በጣም ውጤታማ ነው፤ ሚሊየኖችን ሚሊየነር አድርጓል›› ሲባል የቆየ ቢሆንም አርሶ አደሩ አሁንም እንደድሮው (ወይም ከዚያ በባሰ ሁኔታ) ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ሕይወት በመምራት ላይ ነው፡ ፡ የታየ መዋቅራዊ ለውጥ የለም፡፡ እንደታቀደው እንኳን ግብርናው አድግ ኢንዱስትሪውን ሊመራው ይቅርና ራሱን አርሶ አደሩንም መመገብ አልቻለም፡፡ በአጠቃላይ፣ አንደኛ ዕድገቱ በራስ ሀብት እና/ወይም ባለሀብት የተገኘ አይደለም፡፡ በዚህ ምክንያት በመንግሥትና በብድር ላይ የተንጠለጠለ በመሆኑ ቀጣይነቱ አጠራጣሪ ነው፡፡ ከሁሉ በላይ ደግሞ፣ ዕድገቱ ፍጹም ፍትሃዊ አይደለም፡፡ ከገዥው ኃይል ጋር ንክኪ ያለው ቡድን ፍጹም ባልተጠበቀ ፍጥነት ሲመነደግ አብዛኛው ሕዝብ አሁንም የበይ ተመልካች ነው፡፡ በሀገራችን ባለፉት ሃያ ሶስት ዓመታት ከታዩት አዳዲስ ጉዳዮች አንዱ የፖለቲካ ሥልጣኑን የያዘው ኃይል ራሱን በከፍተኛ ደረጃ በኢኮኖሚው እንቅስቃሴ ውስጥ ማስገባቱ ነው፡፡ በጣም የተደራጀ የፖለቲካ መደብ ተፈጥሯል፡ ፡ ዕድገቱ እንደሚባልለት አይደለም፡፡ እንዲያውም አደጋ ያረገዘ ነው ለማለት ነው፡፡ የፖለቲካው ሁኔታ በእርግጥም የአገዛዙ መሪዎች እንደሚሉት ባይሆንም ሀገራችን የዛሬ ሃያ ሶስት ዓመት ችግር ላይ ነበረች፡፡ ሕዝቡ ለአሥርት ዓመታት ጨቁኖና አስጨንቆ ሲገዛው የነበረው የደርግ አገዛዝ በመውደቁ ቢደሰትም (መደሰቱን ተቃዋሚዎችን በመርዳትና ለአገዛዙ ድጋፉን በመንፈግ ገልጿል) ሽምቅ ተዋጊዎች በያዙት አቋም ላይም ከፍተኛ ጥርጣሬ ነበረው፡፡ በዚህ ምክንያት ብዙ ስጋቶች ነበሩ፡፡ ይህ እውነት ነው፡፡ መረጋጋት የተፈጠረው ግን አሸናፊ የሆነና የታጠቀ ብቸኛ ኃይል (ኢሕአዴግ) በመኖሩ እንጂ እንደሚባለው ሁሉንም ያሳተፈ የሽግግር መንግሥት በመፈጠሩ ቅሬታ ያለው አካል በመጥፋቱ አልነበረም፡፡ በኃይልም ቢሆን ግን ሠላም በመፈጠሩና ኢሕአዴግ ሥልጣን ከጨበጠ በኋላ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ለመመስረት እንደሚሠራ፣ የመደራጀትና የመናገርና የመጻፍ ነጻነትን እንደሚያከብር ወዘተ በመግለጹ ብዙዎች ተስፋቸው ከፍተኛ ነበር፡፡ ይህን ተስፋ አንግበው ወደሀገራቸው የገቡ ብዙ ወገኖችም ነበሩ፡፡ ከእነኝህ ውስጥ አንዳንዶቹ ተመልሰው የአገዛዙ ጠንካራ ተቃዋሚዎች ለመሆን በቅተዋል፡፡ ይህ ሁሉ ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ የኢሕአዴግ መሪዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ በተከሰተው የርዕዮተ-ዓለም ለውጥ ምክንያት ጥርሳቸውን የነቀሉበትን የኮምኒስት (በተለይ “የአልባንያ ሲሻሊዝም”) ትተው ‹‹ነጭ ካፒታሊዝም›› ያሉትን ርዕዮትና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንደሚከተሉ ቢያውጁም ሃቀኛ ለሆነ የመድበለ-ፓርቲ ሥርዓት ፍቅር እንደሌላቸው በብዙ ከመጀመሪያው ጀምሮ ታይቷል፡፡ በሽግግሩ ወቅት ሁሉም ድርጅቶች በፖለቲካ ሂደቱ እንዳይሳተፉ ከማድረግ ጀምሮ የተሳተፉትም ቢሆኑ በልዩ ልዩ

“ከግንቦት ሃያ 1983 ዓ.ም. በኋላ በኢትዮጵያውያን መካከል መለያየት፣ ጥላቻና ቁርሾ ነግሷል፡፡ ዜጎች በኢትዮጵያዊነታቸው በሁሉም አካባቢዎች ተንቀሳቅሰው መሥራት የማይችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ሁሉም በየክልሉ ተጠርንፎና ታጥሮ እንዲቀመጥ ተፈርዶበታል፡፡ ከክልሉ ወጪ የሚሄድ ካለ ያለቦታው እንደተገኘ ይቆጠራል፡፡ ምን ያህል አካባቢውን ቋንቋ ጠንቅቆ ቢያውቅም የመንግሥት ሥራ አያገኝም፤ የቤት መሥሪያ ወይም የንግድ ቦታ አይሰጠውም፤ እንዲያውም ‹‹አካባቢህ አይደለምና ውጣ›› ይባላል”

ጥላቻውና ቂም በቀሉም አለ፡ ፡ የተፈጠረውን የፌደራል አደረጃጀት ተጠቅመው በየክልሉ የከበሩ የመንግሥት ኃላፊዎች እና/ወይም ‹ኤሊቶች› ሕዝቡ እርስ በርሱ እንዲናከስ አበክረው ይሠራሉ፡፡ በዚህ ምክንያት ባልተለመደ መልኩ ብዙ የብሔረሰብ ግጭቶች ተከስተዋል፡፡ አሁንም በብዙ ቦታዎች በቋፍ ላይ ያሉ ግጭቶች አሉ፡፡ ሁሉም በየቤቱ ቂም በቀል እያረገዘ ‹‹እህህ›› ማለት ጀምሯል፡፡ አገዛዙ እንደሚለው ሳይሆን አሁንም ከዩጎዝላቪያ፣ ሩዋንዳ ወይም ሶማሊያ ሁኔታ ብዙም ፈቀቅ አላልንም፡፡ እንዲያውም አሁን ሁኔዎችን ይበልጥ ለመለያየት ምቹ አድርገናቸዋል ማለት ይቻላል፡፡ መለያየቱም በሠላም ሊፈጸም የሚችል አይሆንም፡፡ የቤት ሥራቸውን ያልሠሩ ሀገራት ምን ያህል ዕድገት ቢያስመዘግቡ፣ ምን ያህል የዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ ቢያድግ፣ ግሩም ግሩም መሠረተ ልማቶችን ቢገነቡ፣ ምን ያህል ለረዥም ጊዜ የዘለቀ ሰላም (በጭቆና ውስጥ ያለ ሰላም ሰላም ከተባለ) ከብጥብጥ እንደማያመልጡ እነሊቢያ አሳይተውናል፡ ፡ ትልቅ አብነቶች ናቸው፡፡ ያች ዜጎቿን እየከፈለች ታስተምር የነበረችው ሊቢያ በጎሣ ከአምስት ስድስት ተከታትፋ፣ እነዚያ የሚያማምሩ ወደቦቿና ከተሞቿ ወድመው የጦር አበጋዞች መፈንጫ ሆናለች፡፡ ዜጎቿ በየጎሣው ተቧድነው መተጋተጉን ይዘውታል፡፡ የሶሪያም ሁኔታ ተመሳሳይ ነው፡፡ እኛስ ወዴት እያመራን ነው? አንዳንዶች ኢሕአዴግና ኢሕአዴግ የዘረጋው ብሔረሰብ-ተከል የፌደራል ሥርዓት ለሁለት አሥርት ዓመታት መዝለቁ በራሱ የተዘረጋው ሥርዓት ጥንካሬ እንደሆነ አድርገው ይገልጻሉ፡፡ ይህ ግን በጭራሽ ውሃ የሚቋጥር አመክንዮ አይደለም፡፡ ለመሆኑ ጋዳፊ የሚመሩት ሥርዓት ለስንት ዘመን ኖረ? የአሳድ ቤተሰቦች የሚመሩት ጨቋኝ ሥርዓት ለስንት ጊዜ ቆየ? ራሳችንን ካላሞኘን በስተቀር መንገዳችን እጅግ ፈታኝና ተስፋ አስቆራጭ እየሆነ ነው፡፡ ለዚህ ነው ግንቦት ሃያ መጣልን ወይስ መጣብን ብሎ መጠየቅ አስፈላጊና ወቅታዊ የሚሆነው፡፡ ከዋቢዎች 1. ኢሕአዴግ፣ ዴሞክራሲና ዴሞክራሲያዊ አንድነት በኢትዮጵያ (1997 ዓ.ም.) 2. ኢሕአዴግ፣ አገራዊ ለውጦች ቀጣይ ፈተናዎችና አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ መፍትሔዎች (2000 ዓ.ም.) 3. Oktay F. Tanrisever, why are Federal arrangements not a panacea for containing ethnic nationalism? Lessons from the post-soviet Russian experience (2009) 4. ገብሩ አስራት፣ የኢሕአዴግ አብዮታዊ ዴሞክራሲና ችግሮቹ (2002) 5. Samuel Huntington, political Development in Ethiopia: a peasant based dominant party democracy (1993)

ፊቸር መንገድ ከሂደቱ እንዲወጡ ተደርጓል፡፡ ከቀዝቃዛው ጦርነት ማብቃት በኋላ ሊብራል ዴሞክራሲ አሸናፊ ሆኖ በመውጣቱና ምዕራባውያን ሀገራትና የገንዘብ ድርጅቶች ብድርና ዕርዳታን ከዴሞክራሲ/ ዴሞክራታይዜሽን ጋር በማያያዛቸው ምክንያት ኢሕአዴግ ገንነው እስካልወጡ ድረስ የሌሎችን ድርጅቶች መኖር በተወሰነ ደረጃ ይፈልገው ነበር፡ ፡ የምርጫ- አምባገነን የሚባሉትን ሀገራት ፈለግ ሲከተል ቆይቷል፡፡ ኢትዮጵያ ባለችበት ሁኔታ ጠንካራ መንግሥት እንደሚያስፈልጋት እና ያንን ጠንካራ መንግሥት ሊመራ የሚችል ጠንካራ ድርጅት እንደሚያስፈልግ ለኢሕአዴግ መሪዎች ምክር ከለገሱ ምሁራን መካከል የታወቁት የሀርቨርድ ዩኒቨርሲቲ ምሁር ፕሮፌሰር ሳሙኤል ሃንቲንግተን ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ የፕ/ር ሃንቲንግተን ምክር በሃሳብና በተግባር ልዕልናን/የበላይነትን (hegemony) ስለመያዝ እንጂ በጠብ-መንጃ እያስፈራሩ ወይም አንድ ለአምስት እያደራጁ ወዘተ በሁሉም ምርጫ ማሸነፍን አያካትትም፡ ፡ ሌሎች የምርጫ አምባገነኖች እንደሚያደርጉት ሁሉ የኢሕአዴግ መሪዎች የመረጡት ጠንካራ ፓርቲዎችን በጠብ-መንጃ አፈሙዝ ማዳከምና ማጥፋት፣ ለሥልጣን የማያሰጉ ድንክየና የተዳከሙ ድርጅቶች እንዲኖሩ ሁኔታዎችን ማመቻቸትና ወቅቱን የጠበቀ ምርጫ እያደረጉ መመረጥን ነው፡፡ የምርጫ-አምባገነናዊ ሥርዓቱን በአብዮታዊ ዴሞክራሲ፣ በልማታዊ መንግሥት ወይም ደግሞ በአውራ ፓርቲ ወዘተ ሥርዓታት ስም ለመቀባባት ይሞከራል፡፡ አገዛዙ በ1997 ዓ.ም ከደረሰበት አስደንጋጭ ውድድር ወዲህ በርግጎ የወሰዳቸው እርምጃዎች እውነተኛ ማንነቱን የሚያስገነዝቡና የሃሳብ ብዝኃነትን ለማስተናገድ ፍላጎት የሌለው መሆኑን የሚያጋልጡ ናቸው ማለት ይቻላል፡፡ በግሉ መገናኛ ብዙኃንና በሲቪክ ማኅበራቱ ላይ የደረሱትና የሚደርሱት አሉታዊና ዴሞክራታይዜሽኑን የማያግዙ እርምጃዎች ሁኔታውን ይበልጥ ግልጽ ያደርጉታል፡፡ አገዛዙ በዚኸው አስተሳሰብ እየተመራ ዋና ዋና ተቃዋሚዎችን አዳክሞ (ከራሳቸው የውስጥ ችግር ጋር) በምርጫ 2002 ዓ.ም. ማንነቱን በሚያጋልጥ መልኩ 99.9 በመቶ አሸነፍኩ አለ፡ ፡ ብዙዎች ይህን የምርጫ ውጤት ከታዘቡ በኋላ ከምርጫ-አምባገነናዊ ሥርዓት ወደ ብቸኛ ፓርቲ ሥርዓት እየሄድን ነውን ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ስለዚህ ኢሕአዴግ ጨቋኙን አገዛዝ የታገለው ለሕዝብ ነጻነትና ሉዓላዊነት እንደሆነ አበክሮ ቢገልጽም ያለፉት ሃያ ሶስት ዓመታት ተመክሯችን እንደሚያስገነዝቡን ከግንቦት 20/1983 ዓ.ም. በኋላም ቢሆን ያው በአምባገነን አገዛዝ ሥር መሆናችን ከመቼውም ጊዜ በላይ ግልጽ እየሆነ መጥቷል፡ ፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከመሻሻል ይልቅ የተለየ ሃሳብ ያላቸውን ወገኖች የማይታገስ፤ የሃሳብ ብዝኃነትን የማይታገስ ደርጅት እየሆነ ነው ማለት ይቻላል፡ ፡ አሁንም እንደ ድሮው በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት ወደ ሀገራቸው የማይገቡ ኢትዮጵያውያን በዓለም ዙሪያ ይገኛሉ፡፡ አሁንም እንደ ድሮው ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ድርጅት መሪዎች ይሰደዳሉ፤ ገለልተኛ ማኅበራት እንዲጠፉ ይደረጋል ወዘተ፡፡ ምናልባት የተቀየረው ጭቆናው ሳይሆን የጭቆናው መንገድ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ችግሩ ‹‹ሠላም ሰፍኗል፤ ልማት ላይ ነን፤ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መሥርተናል፤ በትክክለኛው የህዳሴ ጎዳና ላይ ነን›› ወዘተ በሚባልበት በአሁኑ ወቅት ሀገራችን መስቀለኛ መንገድ ላይ መሆኗ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ወዴት? ‹‹ኢሕአዴግ ወደ ሥልጣን በመምጣቱና ትክክለኛ ስትራቴጂ በመከተሉ ምክንያት ኢትዮጵያ ብዙዎች እንደገመቱትና እንደጠበቁት እልቂት አልተከሰተም፡፡ ሀገሪቱም እንደነ ዩጎዝላቪያ፣ ሩዋንዳ ወይም ሶማሊያ አልሆነችም፡፡›› ይላሉ የኢሕአዴግ ሰዎች፡፡ ኢትዮጵያ ከግንቦት ሃያ 1983 ዓ.ም. ወዲህ በዘረጋችው የፌደራል ሥርዓት ምክንያት ሠላም እንዳገኘች፣ በሕዝቡ መካከል ዴሞክራሲያዊ አንድነት እንደተፈጠረም ይነገራል፡፡ አሁን የአፈጻጸምና ዴሞክራሲው ታዳጊ በመሆኑ ምክንያት እዚህም እዚያም ከሚፈጠሩ ጥቃቅን ግጭቶች በስተቀር ችግር እንደሌለ፣ ሀገራችን በህዳሴ ጉዞ ላይ ስለመሆኗም በብዛት ይወራል፤ ይጻፋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያን የገጠማት አደጋ ልክ እንደድሮው አንድ ጨቋኝ አምባገነናዊ አገዛዝን መሸከሟ አይደለም፡፡ የወቅቱ ችግር በእጅጉ ከዚያ ያልፋል፡፡ ሁሉንም ዜጋ ሊያሳስበው የሚገባም ነው፡ ፡ ግንቦት ሃያ ሕዝቡ ከአንድ አስከፊ አምባገነናዊ አገዛዝ ተላቅቆ ወደተሻለ አገዛዝ የተሸጋገረበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው ለማለት አይቻልም፡፡ ባለፉት አሥርት ዓመታት የተከሰቱትና አሁንም በመከሰት ላይ ያሉት ሁኔታዎች ይህን አያሳዩም፡፡ ሕዝቡ የጠበቀውን ዴሞክራሲ አላገኘም፡፡ ሲካሄዱ የቆዩት ምርጫዎች በአብዛኛው የአገዛዙ የቅቡልነት ማግኛ ወይም የመግዣ መሣሪያዎች ናቸው፡ ፡ የተሻለ ነጻነትና ውድድር የነበረው የ1997ቱ ብሔራዊ ምርጫም እንደታየው በገዥው ኃይልና በራሳቸው በተቃዋሚዎች ችግር ምክንያት በአሳዛኝ ተደምድሟል፤ እንዲያውም የዚያ ምርጫ ጦስ እስካሁንም ብዙ ችግሮችን እየወለደ ቀጥሏል፡ ፡ ሕዝቡ የተገባለት በነጻነት የመደራጀትና ሃሳቡን በነጻነት የመግለጽ መብቱ አልተከበረም፡፡ አሁንም ጋዜጠኞቸ ይታሠራሉ፤ ይሰደዳሉ ወዘተ፡፡ ይህ ሁሉ ግን የችግሩ በጣም አነስተኛው ክፍል ነው፡፡ ሌላ ሁሉንም ዜጋ የሚያሳስብና ሊያሳስብም የሚገባ የሀገሪቱን በሀገርነት መቀጠል አለመቀጠል የሚመለከት ችግር አለ፡፡ እንደሚባለው ግንቦት ሃያ የዴሞክራሲያዊ አንድነት መገንባት የተጀመረበት ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ቢሆን መልክም ነበር፡ ፡ ግን አይደለም፡፡ እንደሚባለው ሳይሆን በገቢር እንደሚታየው ከግንቦት ሃያ 1983 ዓ.ም. በኋላ በኢትዮጵያውያን መካከል መለያየት፣ ጥላቻና ቁርሾ ነግሷል፡፡ ዜጎች በኢትዮጵያዊነታቸው በሁሉም አካባቢዎች ተንቀሳቅሰው መሥራት የማይችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ሁሉም በየክልሉ ተጠርንፎና ታጥሮ እንዲቀመጥ ተፈርዶበታል፡፡ ከክልሉ ወጪ የሚሄድ ካለ ያለቦታው እንደተገኘ ይቆጠራል፡፡ ምን ያህል አካባቢውን ቋንቋ ጠንቅቆ ቢያውቅም የመንግሥት ሥራ አያገኝም፤ የቤት መሥሪያ ወይም የንግድ ቦታ አይሰጠውም፤ እንዲያውም ‹‹አካባቢህ አይደለምና ውጣ›› ይባላል፡፡ እንደነዚህ ያሉ እጅግ የበዙ አጋጣሚዎችን ታዝበናል፤ ሁኔታው አሁንም ቀጥሏል፡፡ ቀደም ሲል በናይጀሪያና በሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ስንሰማቸው የቆየናቸው ሁኔታዎች በሀገራችን እየታዩ ናቸው፡፡ ዛሬ በሚያሳዝን መልኩ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ተፈጥሯል በሚባልባት ኢትዮጵያ፣ ከአንዱ ወደ ሌላው ክልል መንቀሳቀስ ልክ ወደሌላ ሀገር እንደመሄድ እየተቆጠረ ነው፡ ፡ እንዲያውም ወደ ሌላ ሉዓላዊ ሀገር የሚሄዱት ወገኖች መብታቸው የተጠበቀ ነው ማለት ይቻላል፡፡ አንዱ አስፈሪ እውነታ ይህ ነው፡፡

ዛሬም! የብሔራዊ ዕርቅ ጥሪ እናሰማለን!

ወቅታዊው ትኩሳት እንደ ግርሻ የሆነው የብሔሮች ግጭት ነው ማለት ይቻላል፡፡ አማራው በኦሮሞው ወገኑ ልጆች አማራ ሆኖ በመወለዱ ብቻ እየተጠቃ ወይም የዘር ጥላቻ ሰለባ እየሆነ ነው፡፡ ጥቃቱም እስከ ግድያ ድረስ በዘለቀ ርምጃ ጭምር እየተገለጸ ነው፡ ፡ በአንዳንድ ሥፍራዎችም ዜጎች የትግራይ ክልል ተወላጅ ወይም በብሔራቸው ትግሬ በመሆናቸው ብቻ የመሰል ጥቃት ሰለባ የመሆናቸው አዝማሚያ መታየቱ ቢያንስ እየተሰማ ነው፡፡ ‹‹ከክልሌ ውጣልኝ! ወደ መኖሪያ መንደርህና ወደ ትውልድ ቀዬህ ተመለስ! በእኛ ክልል ያፈራኸው ሀብትና ንብረት የአንተ አይደለምና እርቃንህን ቅር! ነፍስህን በጨርቅ ቋጥረህ የመውጣት መብት ብቻ ነው ያለህ…›› የሚለው ግፊትና ትንኮሳ እያሰለሰም ቢሆን ወዲያና ወዲህ እየተፈፀመ ለመሆኑ ሰሚ ያጡት የሰለባዎቹ ድምፆች በራሳቸው ማስረጃዎች ናቸው፡፡ እኛ ደግሞ እንዲህ ዓይነቱ ድርጊት በኢትዮጵያ ውስጥ ተፈጽሞ መገኘቱ ብቻ ሳይሆን መሰማቱ በራሱ እጅግ በጣም አሳሳቢ ነው እንላለን፡፡ ከፍ ሲል የገለጽነው ችግር እስከዛሬ ድረስ ወጥ የሆነና ተመልሶም እንዳያገረሽ የሚደረግበት ርምጃ ያለመወሰዱ ጉዳይ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ ከድርጊቶቹ መደጋገምም ይሁን አሁን አሁን እየተባባሱ የመጡበትን ሁኔታዎች ከማስተዋላችን አኳያ የሚከተሉትን ጥያቄዎች መልሰን ማንሳት ተገቢ መስሎ ታይቶናል፡ ፡ እውን በአንዳንድ አክራሪ ብሔረተኛ በሆኑ የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች ‹‹ መናጢ ደሀና አሮጌ ውራጅ ለባሽ እንኳን ቢሆን መንፈሰ ኩሩና ሌላውን በንቀት የሚመለከት ዘር ነው…›› ተብሎ የተፈረጀው አማራ፤ የኦሮሞው ወገኑ ጠላት ነው? በሌሎች ወገኖቹስ ላይ ‹‹ ጭቁን፣ቢሮክራት፣ነፍጠኛ…›› ተብሎ የሚፈረጀው አማራ፤ ከማንም እና ከምንም የበለጠ ባለጋራ ነው? ለመሆኑ አማራ የሚባለው ብሔረሰብ ተወላጅ የሆነው የኢትዮጵያ ሰው፤ አማርኛ ቋንቋን ከመናገር ውጪ ሌላ የመግባቢያ ቋንቋ ባለቤት ያልሆነው ኢትዮጵያዊ ጭምር፤ እንደ ‹‹ብሔር ብሔረሰብ ሕዝቦች መብት›› ሁነኛ ተጻጻሪ ሆኖ በአንዳንድ ጽንፈኛ ብሔረተኞች የሚፈረጀውና በዚህም አጓጉል ፍረጃ ምክንያትነት ዘወትር በጥርጣሬ የሚታየው ለምንድን ነው? መጽሔታችን ይህን የመሰለውን ጥያቄ መልሳ የምታነሳው፤ የጥላቻው ፖለቲካ የሁላችን ሀገር የሆነችውን ኢትዮጵያ ፍፁም ወደማንጠብቀውና በቀላሉም ወደማንቆጣጠረው ወይም መፍትኄ ወደማናገኝለት ቀውስ የሚመራን መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት ብቻ ነው፡፡ ምናልባትም እንዲህ ብሎ ማለት ‹‹እሳት ማቀጣጠልና ነገር ማራገብ ላይ ያተኮረ የግሉ ፕሬስ ተግባር ነው…›› ተብሎ የሚያስተቸን እስካልሆነ ድረስ፡፡ ለሁሉም ከወዲሁ በብሔራዊ ዕርቅም ይሁን በሌሎች የቅድመ ችግር ማስወገጃ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ስልቶች፤ የገዥው ፓርቲ ተሳትፎ ባለበት ሁኔታ ነገ ወይም ዛሬ ሳይባል መድኃኒት የሚያስፈልገው ወቅታዊ ትኩሳት ነው አንደኛው ኢትዮጵያዊ ሰው ሌላውን ኢትዮጵያዊ ዜጋ በቋንቋውና በዘሩ… ምክንያት ለማጥቃት የሚነሳሳበትና የሚያደባበት አዝማሚያ ነው ብለናል፡፡ ስለሆነም በአገራችን ጥልቅና የማያዳግም መፍትኄ ከሚያስፈልገው ወቅታዊ ትኩሳት አኳያ በተሰማበት አካባቢ ተግባራዊውም ሆነ አልሆነ፤ በቅርቡ ከወደ ሱዳን ካርቱም የተሰማው ደስ የሚያሰኝ ዜና ነው እንላለን፡፡ የተሰማው ዜና ዋንኛ ትኩረት ብሔራዊ ዕርቅን የሚጠይቅ መልዕክት ያቋተ እንደመሆኑ ‹‹በእኛም ሀገርና መንግሥት በሆነ›› ያስብላል፡፡ በድጋሚ አደረጉትም አላደረጉት፤ ዘግይተውም ቢሆን ፕሬዚዳንት ጄነራል አልበሽር ያሰሙት የብሔራዊ ዕርቅ ጥሪ፤ ለኢትዮጵያ በጎውን ነገር ለሚመኙ የሰው ዘሮች በሙሉ የመንፈሳዊ ቅናትን ክብሪት በአዕምሮ ውስጥ የሚያጭር ነው፡፡ መቼም ይሁን መቼ እስካልደረሱብን ድረስ፣ ካልተነኮሱን፣ ካልነካኩን፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ከቤት እስከ አደባባይ የሚስተዋለውን የነገር ፍም፣ ቤኒዚንና ነፋስ እየሰጡት ዝንተ-ዓለም የሚቀጣጠል እሳት እንዲሆን የሤረኛነት ሥራ እስካልሠሩብን ድረስ፤ የጎረቤት ሀገሮቻችንን፣ የሕዝባቸውና የመንግሥታቸው ሁለንተናዊ ሰላም፤ የእኛም ሰላም ነው፡፡ መግባባታቸውና ፍቅራቸውም በእነሱው ሊወሰን የሚችል አይደለም፡፡ ቢያንስ የዕርቀ-ሰላማቸው ካፊያ እኛንም ያረሰርሰናል ብለን እናምናለን፡፡ ስለዚህም አሁን ካለንበት አሳሳቢ ሁኔታ አንፃር ከወደ ካርቱም የተሰማው ዜና አዲስ አበባም ላይ በእኛ ባለሥልጣኖች ቢደገም መልካምነቱ ለገዥዎችም ይሁን ለተገዥዎችም ነው፡፡ የሱዳን መንግሥትና የመንግሥቷም ወሳኝ ሰው የሆኑት የአልበሽር የብሔራዊ ዕርቅ ጥሪና የፖለቲካ እሥረኞችን ሁሉ ለመፍታት የመወሰን እርምጃ፤ የካርቱም ዕልቂትና ውድመት ጠሪ ፖለቲካዊ ግለት ማብረጃ ብቻ ሳይሆን፤ የመላው አፍሪካ ቀንድ በይበልጥም የኢትዮጵያ፣ የሶማሌያ፣ ችግሯን ለማመቅ የምትንደፋደፈው የኡጋንዳ፣ ከእናት ሀገሯ በ ‹‹ናጽነት›› ስም ተለይታ በፖለቲካዊ የነገር ማብለያ ምድጃ ላይ በመጣድ ለምትንጨረጨረው ኤርትራ ወቅታዊ ትኩሳት ማቅለያ የሚሆነውን መድኃኒት አመላካች ጭምር ነው የሚል ዕምነት አለን፡፡ በመሆኑም ይኼን ከወደ ካርቱም የተሰማን እና ሱዳንን የመሰለ ሀገር በሀገርነቷና በመንግሥትነቷ ሊያስቀጥል የሚያስችል፣ የሚጣሉት ዝሆኖች መፈንጫና የደም ጥማት ማርኪያ ሆኖ ለሚቀርበው ወንድም የሱዳን ሕዝብ ዘለቄታዊ ሰላምን ብቻ ሳይሆን ከዘለቄታዊ ሰላሙ ሊያገኝ የሚችለውን የዕድገትና የብልፅግና …ፍሬ ተቋዳሽ ሊያደርገው የሚያስችለውን የብሔራዊ ዕርቅ ጥሪንና የፖለቲካ እሥርኞችን በሙሉ ከእስራት ነፃ የማድረግን ያህል ዜና መስማት፤ ሌላው ቢቀር ‹‹እንደዚህ ዓይነቱን ይበል የሚያሰኝ ነገር ለእኛም ባደረገው…›› የሚል ቀና ስሜት፤ እናት ሀገራችን ኢትዮጵያ ከጦርነት፣ ከጥፋት፣ ከውድመትና እርስ በእርስ በነገር ከመቋሰል አዙሪት እንድትወጣ ሌት ተቀን ከልባቸው አጥብቀው በሚመኙ ዜጎች ዘንድ እንዲጎለብት የሚያደርግ፤ ወቅታዊ ጉዳይ፣ ወቅታዊ ትኩሳትም ብለን ማመናችን በራሱ ችግር ያለው ሆኖ አይሰማንም፡፡ ዓመታት ያልፈቱት ችግር ያለፉትን ዓመታት ፖለቲካዊ ስንክሳሮች ስንመረምራቸውም ሆነ የአሁኑን ሁኔታ እያስተዋልን ስለመፃኢው ጊዜ ስናሰላስል፤ ኢትዮጵያ ባለቤት ያጣች ሀገር ሆና የምትታየን መሆኑን አንክድም፡፡ ‹‹አገሪቱ የማን ነች?›› ተብሎ ሲጠየቅ በቃል ደረጃ በቅፅበት የሚከሰተው መልስ ‹‹የዜጎቿ ሁሉ›› የሚለው ነው፡፡ ከመኖር ከተገኘው እውነትም ይሁን በየዋህነትም ይባል በተላላነት… ፀንቶ ከኖረው ዕምነት አኳያ ‹‹ኢትዮጵያ የኢትዮጵያውያን ሁሉ›› የመሆኗ ሐቅ፤ አሁንም በቃል ደረጃ የሚያሻማ አይደለም፡፡ ከቅድመ 1983 ዓ.ም በፊት በነበረው ሁኔታ፤ ሀገሪቱ የኢትዮጵያውያን ዜጎች ሁሉ (የኦሮሞው፣ የአማራው፣ የትግሬው፣ የአፋሩ፣ የሱማሌው፣ የወላይታው፣ የጋምቤላው፣ የሸኰው፣ የመዠንገሩ፣ የኮንሶው፣ የከንባታው፣ የአደሬው፣ የአገው፣ የሺናሻው…) ‹‹ነች›› መባሉ፤ በማለት ደረጃ የሚያስማማ ነበር፡፡ በኑሮ ደረጃ፣ በኢትዮጵያ ሀብትና ፀጋ የበለጠ ተጠቃሚ፣ የበለጠ ተገልጋይ የበለጠ ወሳኝ፣ ሰጪና ነሺ፣ አድራጊና ፈጣሪ… በመሆን ደረጃ ግን በተግባር የሚታይ ዜግነታዊ ልዩነት ነበረ፡ ፡ ይህ ‹‹ነበረ›› የምንለው ልዩነት ከዚያም በቀደመው ጊዜ የነበረ እንደመሆኑ መጠን፤ ዛሬ ደግሞ ቅርፁንም ይሁን መልኩን ለውጦ በችግርነቱ ቀጥሏል፡፡ ይልቁንም ‹‹ኢትዮጵያዊነትን›› በራሱ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ከማስገባት ተንደርድሮ፤ ጎሣን ወይም ነገድን፣ ብሔርን ወይም ብሔረሰብን በራሱ እንደዜግነት ወደ መቁጠሩ ወይም ወደ መውሰዱ የአክራሪነትም እንበለው የዘረኛ ጽዮናዊነት ጽንፍ እያመራ ይገኛል፡፡ ይህ እያመራ ያለው ሀገራዊ እውነት፣ ማንም ወደደው ወይም ጠላው በዛሬይቱ ‹‹ፌዴራላዊት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ›› ከዳር ምድር እስከ መሀል መዲና በግልፅ የሚታይ ነው፡፡ የመታየቱም ምክንያት በኢትዮጵያ ለዓመታት ያልተፈቱት ፖለቲካዊ፣ አስተዳደራዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊ፣ ሕጋዊና አስተሳሰባዊ ችግር ሰፍኖ መኖሩን ብቻ ሳይሆን ዛሬም ችግሩ ‹‹እየተቀረፈ ነው…›› ቢባልም እንኳ በይበልጥ መወሳሰቡንና ከናካቴውም ውሉ እንደጠፋበት ልቃቂት መሆኑን አመላካች ነው፡፡ በእንደዚህ መሰሉ መለኪያ የኢትዮጵያ አጠቃላይ ሁኔታ፤ ዓመታት ያልፈቱት፣ ይልቁንም ከመጥበሻው ወደ እሳቱ እያመራ የሚገኝ ችግር መሆኑ፤ ከመፃኢው የከፋና አይቀሬ የሚሆን አደጋ እናመልጥ ዘንድ ብሔራዊ ዕርቅን እንመኝ ዘንድ የማያስገድደን ነው ሊያሰኝ አይችልም፡፡ እንደሚስተዋለው በኢትዮጵያችን እጅግ በጣም ብዙ ፖለቲካዊ ጥያቄዎች ‹‹ነበረ›› የሚባለውን ‹‹ብሔራዊ ጭቆና›› ለማስወገድ ‹‹ያስችላሉ›› በሚል ተነስተዋል፡፡ መነሳት ብቻ አይደለም ‹‹በሕገ-መንግሥቱ እና በሕገ- መንግሥታዊ ሥርዓቱ›› ቡራኬ፤ ለተነሱትና ‹‹መልካም አማራጭ ናቸው›› ለተባሉት ‹‹ዴሞክራሲያዊ›› ለተባሉ ጥያቄዎች ‹‹ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ›› የተባለ መልስ ተሰጥቷል፡፡ መልሱን እንዲያስፈፅሙ ወይም ተግባራዊ እንዲያደርጉም፤ የነገው ሁነት በትላንቱ እና በመፃኢው ጥሩ መነፅር ለሚመለከቱ ሩቅ አሳቢዎች… ሳይሆን በሌላው ውድቀትና መዋረድ የራሳቸውን ማንሰራራትና ክብር ብቻ ለሚመዝኑ፣ ‹‹እኔ ከሞትኩ ሠርዶ አይብቀል›› ለሚሉ፤ ምርኮኛና በልቶ አደር ፖለቲከኞች ሥልጣንና ኃላፊነቱ ተሰጥቷል፡፡ እንደዚህም ስለተሰጠና የአፈፃፀሙንም ሁኔታ ለማረምና ለማስተካከል ‹‹ዓባይን በጭልፋ›› ወይም ‹‹ቁጭ ብለው የሰቀሉትን….›› እየሆነ አስቸግሯል፡፡ ስለአስቸገረም ‹‹ዴሞክራሲያዊና ሕገ- መንግሥታዊ መብታችንን እንዳሻን የመተርጎም ነፃነት ተጎናፅፈናል…›› በሚሉ ተላሎችና አውቆ አጥፊዎች ርምጃ፣ ጥቂት የማይባሉ የሀገሪቱ ዜጎች ‹‹የእኛም ናት…›› በሚሏት ኢትዮጵያ ውስጥ ‹‹የዚህ ወይም የዚያኛው ክልል ተወላጅ ናችሁ አይደላችሁም…›› በሚል ምክንያት፤ የገዛ አገራቸው ተፈናቃይ፣ ስደተኛና ‹‹አቤት…›› ቢሉም መልስ የማያገኙ ዜጎች ሆነዋል፡

…እኛ በአብዛኛው (ሰዋዊ ባሕሪ ነው ቢባልም) ትላንት አውቆም ይሁን ሳያውቅ… የጎዳንን፣ ‹‹በእንጀራችን ላይ ቆሞ ነበር…›› የምንለውን፣ የመሰከረብንን፣ የተኮሰብንን፣ ያስተኮሰብንን፣ አንድ ጥቅም ያሳጣንን ወይም ያጓደለብንን ብቻም ሳይሆን ‹‹እንደዚያ ለማድረግ አስቦ ነበር ወይም ከማድረግ የማይመለስ ሰው ነበር›› በማለት የምንገምተውን ወይም የምንጠረጥረውን ዜጋ፤ ገብቶትም ይሁን ሳይገባው…

፡ የእንደዚህ ዓይነቱም ሁነት ግፊት የሀገሪቱ ‹‹ዳር አገር…›› ናቸው ከሚባሉት አካባቢዎች እየተነሳ አድማሱን በማስፋፋት ለአዲስ አበባ ከተማ እጅግ ቅርብ በሆኑትና እንደ አምቦ ባሉት የኢትዮጵያዊነት ማዕከሎች ሳይቀር በተግባር መታየት ጀምሯል፡፡ ይህ አሳሳቢና ፍፁም አስጊ ሊሆን የሚችል ‹‹የዴሞክራሲያዊ መብት›› አተገባበር በአምቦ ሲፈፀም ከታየ፣ እነ አቶ ፀጋይ ዳምጤን ከዳኖ ወረዳ … ካፈናቀለ፣ ለመደብደብ፣ ለእንግልት ካደረገ፤ ከዚህም አልፎ ተርፎ ለአንድ ሰውም ቢሆን በዘር የተነሳ ለሕይወት መጥፋት ሰበብ ከሆነ፤ በአምቦ የተፈፀመው ነውረኛ ድርጊት ነገ ወይም ዛሬ ‹‹ፊንፊኔ የኦሮሞ ነው!…›› በሚል ሰበብ በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ ላለመሆኑ ምን ዓይነት መተማመኛ ማግኘት ይቻላል? የስጋቱ ጉዳይ ከሆነ ምልክቱ እየታየ ነው፡፡ አንዳንድ ግለሰቦች፤ ነገር ግን ሊናቁ የማይገባቸው የኦሮሞ ልጆች ከወደ ዳር ሀገር ተቀምጠውም ይሁን በቅርብ ሆነው በውክልና የሚያስተዳድሩትንና የሚያዙበትን ቤትና ንብረት ‹‹ለምን ለአማራ አከራያችሁት? ለምንስ ነፍጠኛ እንዲገለገልበት ታደርጋላችሁ?…›› በማለት፤ ውክልናውን በሰጧቸው ወዳጆቻቸው ወይም የቤተሰቦቻቸው አባላት ላይ ተግሣጽና ቁጣ አዘል ማስጠንቀቂያ ሲሰጡም ‹‹ሆደ ሰፊው›› የአገራችን ዜጋ ሰምቶ እንዳልሰማ ሆኖ እያለፋቸው ነው፡፡ ታዲያ ይኼን የመሰለው ቀላል የሚመስል ግን ቀላል ያልሆነ፣ ብልጭ ድርግም ሲል… የሚስተዋል፤ ነገር ግን ውስጥ ውስጡን የሚፍምና የሚግም ከዘረኛው ፖለቲካ ማህፀን የሚቀፈቀፍና ዓመታት ያልፈቱት ችግር፤ በብሔራዊ ዕርቅ መውረድ አማካይነት ማርከሻ የማያስፈልገው ነው አይባልም፡፡ በበቀል መንገድ ላይ ያለ ጥርጥር ኢትዮጵያን እዚህ ያደረሰው መንገድ ጤነኛ አልነበረም፡፡ ‹‹ኧረ ጤነኛም ነበር…›› ከተባለ፤ የኢትዮጵያ ታሪክ በአብዛኛው ‹‹የጦርነት ታሪክ ነው›› ባልተባለ ነበር፡፡ እዚህ ያደረሰን መንገድ ጤነኛ ባለመሆኑ የተነሳ፤ የመንግሥትነትና የአገር ገዥነት ሥልጣኑ በጉልበት እየተያዘ፣ በጦርነት የሚቀማና በነፍጥና በነፍጠኞች ብዛትና ኃይል እየተጠበቀ ለዝንተ ዓለም ፀንቶ የሚቆይ እየመሰለ ቀጥሏል፡፡ ኢትዮጵያ የሦስት ሺህም፣ የመቶ ዓመትም ይሁን የሉሲን … ያህል የመንግሥትነትና የሀገርነት ታሪክ ይኑራት፤ የተጓዝንባቸው መንገዶች በአያሌው ወደ ጦርነትና ወደ ውድመት የመሯት የበቀል መንገዶች ናቸው፡፡ እንዲህ ብሎ ማለት፤ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ በአንደኛውም ወቅት ቢሆን ከበቀልና ከቂመኝነት አዚም የፀዳ የዕርቅና ከልብ ለመግባባት የመፈለግ፣ በወንድማማችነትና በእህትማማችነት የመተያየት፣ ተከባብሮና ተፋቅሮ የመኖር ስሜት የተንፀባረቀበት አንድም የታሪክ አጋጣሚ አልተፈጠረም ማለት አይደለም፡፡ የቅርብ ጊዜው የሀገርነትና የመንግሥትነት፣ የገባሪና የአስገባሪነት፣ የገዥና የተገዥነት ዶሴያችን እንደሚመሰክረው እውነት ከሆነ ግን፤ ዛሬ ላይ ያደረሰን የበቀል መንገድ ነው፡፡ ከቤተሰብ እስከ ማኅበረሰብ፣ ከማኅበረሰብ እስከ ላይኛው መንግሥታዊ ቅርፅ ድርስ፤ አመለካከቱ ‹‹ልኩን አሳየዋለሁ!…›› በሚለው ጉልበትንና ኃይልን በተከታዩ ላይ ከማሳየት ፍላጎት ወይም ከበቀል ዕንቁላል ከሚፈለፈልና አስተማሪ መሆን ከማይችል መርህ የሚመነጭ ነው፡፡ እኛ በአብዛኛው (ሰዋዊ ባሕሪ ነው ቢባልም) ትላንት አውቆም ይሁን ሳያውቅ… የጎዳንን፣ ‹‹በእንጀራችን ላይ ቆሞ ነበር…›› የምንለውን፣ የመሰከረብንን፣ የተኮሰብንን፣ ያስተኮሰብንን፣ አንድ ጥቅም ያሳጣንን ወይም ያጓደለብንን ብቻም ሳይሆን ‹‹እንደዚያ ለማድረግ አስቦ ነበር ወይም ከማድረግ የማይመለስ ሰው ነበር›› በማለት የምንገምተውን ወይም የምንጠረጥረውን ዜጋ፤ ገብቶትም ይሁን ሳይገባው… ያላጨበጨበልንን፣ ያልፈከረልንን፣ ያልሳቀልንን …ወገን፤ በጨዋነትና በትህትና፣ በአስተዋይነትና በብልሃት፣ በመተውና በመርሳት፣ ከዛሬው በጣም ጥሩ አጋጣሚ ለነገ እጅግ በጣም ብዙ ትርፍ ሊያስገኝ በሚችል ጥበብ ለማስተማር የምንፈልግ ወይም ተነሳሽነቱ ያለን አይደለንም፡፡ ዛሬ ደግሞ ልክ እንደትላንቱ ያለፈው እየተናፈቀ የአሁኑ የሚረገምበት ብቻ አይደለም፡፡ ዛሬ ባለወር ተራው ያለፈውን ሥርዓትና የሥርዓቱን አራማጆች ብቻ ሳይሆን ‹‹ተቀናቃኝ ናቸው›› የሚላቸውን ሁሉ፤ ከማውገዝ፣ ከማጥላላት፣ ከመወንጀልና ወህኒ ከማውረድ አልፎ ራሱንና ራሱን ብቻ የተቀደሰና ፍፁም የተሻለ አድርጎ በመስበኩ ተግባር ተጠምዶ የሚታይበትም ነው፡ ፡ ዛሬ ‹‹ተቃዋሚ›› ወይም ‹‹የሥርዓት ለውጥ ናፋቂ›› የሚባለው የፖለቲካ ድርጅትም ቢሆን በውስጡ እርስ በእርስ፣ በውጪ አንደኛው ከሌላው፣ በጋራ ደግሞ ሁሉም ከገዥው ፓርቲና መንግሥት ጋር የሚናከስና ‹‹ጠብና ልዩነት›› አለኝ ባይ ነው፡፡ የዚህ ሁሉ ዛሬ መነሻው የበቀልተኝነት ዘር የሆነው ቂመኝነትና ከፍፁም በራስ ያለመተማመን ስሜት የሚመነጨው ተጠራጣሪነት ብሎም ራስን ከሌላው አልቆ በማክበር የመኮፈስ አዝማሚያ ሲሆን፤ መዳረሻው ደግሞ ጦርነት፣ ውድቀትና ትንሳዔ አልባው ሁለተናዊ ሞት ነው፡፡ ይሄን በመሰለው የበቀል መንገድ ላይም፤ ደርጎች ብቻ ሳይሆኑ ኢሕአፓዎች፣ መኢሶኖች፣ አንድነቶች፣ መኢአዶች፣ ሕብረቶች፣ ቅንጅቶች፣ ኦነጎች፣ ኢሕአዴጎች ….ብዙ ርቀት ተጉዘዋል፡ ፡ ዛሬም ከራሳቸውም ጋር ይሁን ከሌላው ወይም ከባላንጣዎቻቸው ጋር አልታረቁም፡፡ አንዳንዶቹ ታሪክ ራሱና ትውልድ ድብን አድርጎ እስኪታዘባቸው ድረስ፤ የጋራ በሚሆን ባላንጣቸው ተደምስሰው ባለፉበት ሁኔታ እንኳን፤ መካሰስና መወነጃጀላቸውን አላቆሙም፡፡ እስከደም መቃባት ደረጃ ካደረሳችው ፖለቲካዊ ሥልጣን ብዙ ሺህ ኪሎ ሜትር ርቀውና ‹‹እንሞትልሻለን…›› ያሏትን ሀገር በፉክክር አፍርሰው ካበቁም በኋላ፤ ህሊናቸው ልጣቸው መራሱን፣ ጉድጓዳቸው መማሱን እየነገራቸውም ቢሆን የመረጡት በበቀል መንገድ ላይ መረማመዱን ነው፡፡ የኢትዮጵያ አድባርና አውጋር ግን፤ ወደ ደም መፋሰሱና ወደ ርስ በርስ ዕልቂቱ… የሚያሳልፈው ከተንበሪ ( መዝጊያ ) ተዘግቶ የሚያይበትን ቀን በመናፈቅ፤ ካርቱም ላይ የተሰማው የብሔራዊ ዕርቅ ጥሪ፤ ከኢሕአዴጋዊው ቤተ-መንግሥትም እንዲመነጭ የሚማፀን ይመስላል፡፡ ምን ይሻለናል? የሚሻለን ዛሬም ብሔራዊ ዕርቅ ነው፡፡ የሚሻለን ቂም የሚያርቅ፣ ደም የሚያደርቅ ብሔራዊ ዕርቅ በኢትዮጵያ እንዲወርድ መመኘት ብቻ አይደለም፡ ፡ ለተግባራዊነቱም ከልብ መትጋት ነው፡፡ ለዓመታት የዘለቁትንና ከድጡ ወደ ማጡ እያመሩ ያሉትን የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ችግር ለማስወገድ፤ የሚኖረው የተሻለና አማራጭ የማይኖረው ምርጫ ብሔራዊ ዕርቅ ለማውረድ ዝግጁ መሆን ነው፡፡ ዝግጁነቱም ያልተንዛዛ ሰበብንና ጊዜ ቀጠሮን ይሻል፡፡ በዚህ ገረድ የሚኖረውን የበለጠ ድርሻ ማንሳት የሚኖርበት ደግሞ፤ እንደ አልበሽር መንግሥት ሁሉ፤ በሕወሓት ኢሕአዴግ የሚዘወረው የአቶ ኃይለማርያም አስተዳደር ነው፡፡ አስተዳደሩ በክፉ ከሚነሳበት ‹‹የአገዛዝ ባሕሪው›› እና ዕርቅን ከሚጠየፈው መጥፎ አዚሙ ተላቆ በተጨባጭ የሀገርና የመንግሥት አስተዳዳሪ መሆኑን ለማሳየት፣ ለራሱም ይሁን ለኢትዮጵያ የሚበጀውን መስመር በቁርጠኝነት ለመከተል …በሆደ ሰፊነት የብሔራዊ ዕርቁን አይቀሬነት የሚያበስረውን የጥሪ ደወል ለመደወል፤ ነገ ሳይሆን ዛሬ ከነበረ ማንነቱ ጋር ተወያይቶ ከአንድ ውሳኔ ላይ መድረስ አለበት፡፡ የነፍጥ አምልኮ ሲያበቃ፣ የትምክህተኝነት ፖለቲካዊ ውርስ ሲያከትም፤ በይበልጥ የሚጠቀመውና ከበቀል መንገድ ጉዞው ኪሣራ ነፃ የሚሆነው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መሆኑን በመገንዝብ፤ የሕወሓት ኢሕአዴግ መንግሥት የፖለቲካ እሥርኞቹን ‹‹አሟጦ›› በመፍታትና የብሔራዊ ዕርቅ ጥሪ በማስተላለፍ አዲስና በኢትዮጵያ የትንሳዔ ዘመን የታሪክ መዝገብ ላይ ስሙን በደማቅ ቀለም የሚያፅፍ አስመስጋኝ ተግባር ማከናወን ይጠበቅበታል፡፡ ለኢትዮጵያው መንግሥት የሚሻለው ከፍ ሲል የተገለጸው ነው፡፡ እርስ በርሳቸው ለሚወነጃጀሉት፣ የሀገሪቱን እና የሕዝቧን የጣዕር ዘመን በመነካከሳቸው ብዛት ለሚያረዝሙት ስመ ተቃዋሚዎችም ቢሆን ለብሔራዊ ዕርቅም ይሁን ከየራሳቸው ጋር ለመታረቅ፤ ከዛሬ የተሻለ ቀን፣ ከዛሬ የተሻለ ሰዓት፣ ከዛሬ የተሻለ ዕድል የላቸውም፡፡ ለግራ ቀኙ ወገን የተሻለው ነገር ይኸውና ይኸው ብቻ ሲሆን ከዚህ ውጪ ያለው፣ ሊኖር የሚችለውና የሚታየው መንገድ ሁሉ ግን፤ እስከዛሬ ኢትዮጵያ ‹‹ይበጀኝ ይሆናል…›› እያለች ወይም ‹‹ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ለመሆን ያበቃታል…›› እየተባለላት ወደ አዘቅት የምትወርድበት የቁልቁለት መንገድ ነው፡፡ ልማትም ቢሆን ብዙኃኑ አብሮ በኑሮው መሻሻል፣ በተስፋው መለምለም፣ በአብሮነቱ ፍቅር ያለ አንዳች ስጋት ከነአዕምሮው መልማት ሲችል እንጂ በፎቅ ክምርና በጥቂቶች ማበጥ የሚመዘን ወይም የሚለካ አይደለም፡፡ ስለዚህ የሚሻለው አብሮ በጋራ በሁለንተናዊ መስክ መልማት ነው፡፡ ወደዚህ የሚያደርሰውም ለዓመታት ያልተፈቱትን ችግሮች የሚቀርፈው፣ በበቀል መንገድ ላይ ከምናደርገው አጥፊ ጉዞ ሊያቅበን የሚችለው፣ ኢትዮጵያን በሀገርነቷ የማስቀጠል ዋስትና የሚሆነው፣ አመንም አላመንም በሀገሪቱ አየር ላይ የሚያንዣብበውን የሕዝባዊ አመፅ ደመና በመግፈፍ ዳግመኛ ሠይፍ ከምንማዘዝበት ሜዳ እንዳንወርድ የሚገላግለን፤ ዛሬም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ዕርቅ የመውረዱን አስፈላጊነት አምነን በመቀበል ተግባራዊ ስናደርገው ነው፡፡ እጅግ ለሚያስፈልገውና ለብሔራዊ ዕርቁ መውረድ መደላድል የሚሆነውም፤ የፖለቲካ እሥረኞችን መፍታት ነው፡፡ አዳዲስ የፖለቲካ እሥርኞችን ወደ ወህኒ ከማጋዝ መቆጠብ ነው፡፡ ሥልጣንን ለማጋራት፣ አገሪቱን የጋራ ቤት ለማድረግ መወሰን ነው፡፡ በጥሪ ደረጃ የተሰማውን ነገር ግን ከልብ እንዲሆን የሚፈለገውን የአልበሽርን አማራጭ መከተል ነው፡፡ የካርቱምን ጥሪ ‹‹ለእኔም…›› ብሎ መስማት ነው፡፡ አማራጩን ለመከተልና አስደሳቹን ጥሪ ለመስማትም፤ የግድ ኢትዮጵያ ሱዳን የገባችበት የፖለቲካ ማጥ ውስጥ በመግባት ሂሣቧን ካወራረደች በኋላ መሆን የለበትም፡፡ የደቡብ ሱዳን መገንጠልና ገና በጫጉላነት ዘመኗ ወደ ሌላ ዙር ጦርነት ያለፈችበት፣ የረሃብ፣የችጋር፣ የማይነጥፍ የሚመስለው የጠብ ቆስቋሽነት ሁኔታና እንደ ኤርትራ ዓይነቱ ጉዳይ ኢትዮጵያ ውስጥም ተደግሞ መታየት ይኖርበታል አይባልም፡፡ ይህም ክፉ ነገር በሃገራችን ይሆን ዘንድ ኢትዮጵያችን ‹‹የዕብድ ገላጋይ›› ያስፈልጋታል ተብሎ አይተሰብም፡፡ አሁን ላይ ሆኖ የዳርፉርና የአቢዬ ግዛት ውጥረትና ጡዘት ብቻውን አልበሽርን ለብሔራዊ ዕርቅ ጥሪ …ገፋፍቷል ብሎ ማሰብም ትንሽ የማይባል የአመለካከት ጉድለት አለው፡፡ ከእንግዲህ የኢትዮጵያ መንግሥት መሪዎች በጎረቤት ሀገራት ተፈጠረ የሚባለውን ቀውስ ለማስወገድ በሽምግልና ስም መሯሯጥ ብቻ አይደለም የሚጠበቅባቸው፡፡ በቤታቸውም ለነፋስ የተጋለጠ የነገር ፍም መኖሩን ተገንዝበው ሰደዱ ከመቀስቀሱ በፊት የአደጋው ተከላካይ ዳኛ ሆነው የመቆም ህሊናዊም፣ታሪካዊም ኃላፊነት አለባቸው፡፡ በአንቀፅ 39 ላይ የተዋደደው የመጠበቂያ ቀለበት ከተነቀለ የሚያስከትለው መዘዝ ‹‹ጦርነትን እንሠራዋለን…›› ለሚሉት ሰዎች የሚጠፋቸው አይመስለንምና ነው ዛሬም የብሔራዊ ዕርቅ ጥሪ እናሰማለን የምንለው ፡፡

ነውረኛዋና ሰላይዋ ዝማም (ኢየሩሳሌም አርአያ)

June 21, 2014 – ትንታኔ
newregnawa-selayዝማም ትባላለች፤ የሕወሐት ታጋይ ናት። ባለቤቷ አቶ ቢተው በላይ ይባላሉ። ቢተው እስከ1993 ዓ.ም የደቡብን ክልል በበላይነት ሲያሽከረክሩና ሲመሩ የቆዩ ናቸው። በመጋቢት 93 ከአቶ መለስ ጋር በተፈጠረ የፖለቲካ ውዝግብ ከሌሎች ጋር ተነጥለው ወጡ። ከዚያም ከደቡብ ክልል ፕ/ት አባተ ኪሾ ጋር በሙስና ተከሰው ዘብጥያ ወረዱ። ፍ/ቤት መቅረብ እንደጀመሩ ከጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል ጋር ለዜና ዘገባ ስንመላለስ የቢተውን ባለቤት ዝማምን ተዋወቅኳት። በክልል 14 ቢሮ ተመድባ ነበር የምትሰራው። ባለቤትዋ ከታሰረ በኋላ ግን ዝቅ ተደርጋ በቀበሌ ደረጃ ተመደበች። ዝማም በርካታ ምስጢሮችን ታውቃለች። አርከበ ወደ ከንቲባነት ሊመጡ እንደሆነና ሌሎች ቁልፍ መረጃዎችን አቀብላኝ በኢትኦጵ ጋዜጣ ሰርቼዋለሁ።
..ዝማምን ዛሬ እስር ቤት የሚገኘው የደህንነት ሹም ወ/ስላሴና አየር መንገድ ያለው ሃይሌ አጠመዷት። የሕወሐት ነወረኛ ደህንነቶች ጋር መጠጥ እየተጋተች አንሶላ እንደተጋፈፈች ስገልጽ ከልብ እያዘንኩና ይህን ዘገባ ለምታነበው ሴት ልጇ እየተሸማቀቅኩ ነው። ነገር ግን ይህን ነውረኛ ድርጊቷን ባልዋ አቶ ቢተው እስር ቤት ሆኖ ያውቅ ነበር። እቤቱ ውስጥ በፓርቲው አንጃዎች ይካሄድ የነበረ ስብሰባ እየተቀረጸ አቶ መለስ ዘንድ ተልኳል። ይህ ሁሉ በዝማም የተከናወነ ነበር።… ሳይታወቅ የቆየውን “ኢየሩሳሌም አ..” የብእር ስም በመጠቆምና ለነወ/ስላሴ አሳልፋ በመስጠት የግድያ ሙከራ እንዲፈጸምብኝ ያደረገችው ዝማም ናት።
ንጉሴ የተባለ መቶ/አለቃ ተገድሎ ሬሳው ጅብ እንዲበላው የተደረገው በዝማም የሴራ ተባባሪነት ነው። (ታሪኩ ረጅም ሲሆን ይህን ጠንቅቀው የሚያውቁት መጽሃፍ ጽፈው ሲያበቁ ይህን ታሪክ አለማካተታቸው ያሳዝናል) ..እንደ ዝማም ሁሉ ባለቤትዋ ከ6 አመት እስር በኋላ ሲፈታ ያሳየው መገለባበጥ አሳፋሪ ነበር። ከአቶ መለስ ተጠግቶ የአፋር ክልል ባለስልጣን ሆነ። ከዚያም ወደ መከላከያ ኢንጂነሪንግ አመራ።ጭራሽ በዚህ ዓመት በሕወሐት የተፈጠረው ቀውስ “አስታራቂ” ሽማግሌ ሆኖ ተሰየመ። የስብሃት ተከታይነቱንም አረጋገጠ። ባልና ሚስት እጅግ የለየለት ርካሽ ቁማር የተጫወቱ ናቸው። …ባለፈው ሳምንት አንድ ወጣት ልጃቸው በሞት መለየቱን ሰማሁ። ከነርሱ ተግባር ጋር ልጁ የሚያገናኘው ነገር ስለሌለ በመሞቱ ከልብ አዝኛለሁ። ፈጣሪ ነፍስ ይማር!
(ነውረኛዋና ሰላይዋ ዝማም ይህቺ ናት)

በሺህ የሚቆጠሩ አማሮች ከምዕራብ ወለጋ ተፈናቀሉ

June 21, 2014 – ዜና
በሺህ የሚቆጠሩ አማሮች አማራ በመሆናቸው ብቻ ተመርጠው ከምዕራብ ወለጋ ከጊምቢ እና ቄሌም (እንፍሌ ወረዳ አሽ ቀበሌ) ተፈናቀሉ
ጉዳያችን ሰኔ 12/2006 ዓም (ጁን 20/2014)
በብዙ ሺህ የሚቆጠር የአማራ ህዝብ ኢትዮጵያውያን ከምዕራብ ወለጋ ጊምቢ እና ቄሌም በኃይል አካባቢውን እንዲለቁ ከመደረጉ በላይ ድብደባ እናAmhara-People-in-Benshangul-Kilil1ግድያ እንደተፈፀመባቸው ቪኦኤ የአማርኛው አገልግሎት ሰኔ 12/2006 ዓም ምሽት ባስተላለፈው ዘገባ ገለፀ።
ዘገባው የተፈናቃዮችን ምስክርነት እንዳስደመጠው ድብደባው እና ግድያው በከተማው ሕዝብ እና ፖሊስ የታገዘ መሆኑን እና ህይወታቸውን ያተረፉት በኮርኒስ እና ጫካ በመደበቅ መሆኑን ሲገልጡ፣አንድ ምስክርነታቸውን ለቪኦኤ የሰጡ ተፈናቃይ አክለው እንደገለፁት ከጊምቢ ከተማ ብቻ ከሶስት ሺህ በላይ የአማራ ህዝብ ኢትዮጵያውያን መፈናቀላቸውን ተናግረዋል።ሌላው ምስክርነት ሰጪ ደግሞ ቁጥሩን ከስምንት ሺህ ሕዝብ በላይ አድርሶታል።
አምስት ልጆች የነበራቸው መሆናቸውን የተናገሩት ሌላ ተፈናቃይ የነበራቸው መደብር መዘረፉን እና ካለምንም ሀብት መቅረታቸውን፣ጉዳዩን አቤት ለማለት ወደ ባለስልጣናት ቢሄዱም ሰሚ ማጣታቸውን አስታውቀዋል።
የቪኦኤ ጋዜጠኛ ጉዳዩን አስመልክቶ ቀደም ብሎ የአካባቢው የፀጥታ ጉዳይ ኃላፊ የተባሉ እሳቸው ግን የኦሕዴድ ድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ነኝ ያሉ አቶ አወቀ የተባሉ የክልሉ ባለሥልጣን ስለጉዳዩ ሲናገሩ ”ያባረረ የለም’ ሲሉ ተደምጠዋል።
የኦሮምያ ክልል የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳይ ኃላፊ ወ/ሮ ራቢያ ኢሳ ”ሰዎቹ የሄዱት ፈርተው ነው” ካሉ በኃላ ”ቁጥራቸው ”መቶ አይሞሉም ” ማለታቸው ግርምትን ፈጥሯል።የቪኦኤ ጋዜጠኛ አቶ ሰለሞን በመቀጠል ” ቁጥሩ አይደለም ወሳኙ አንድም ሰው ቢሆን ለምን ተፈናቀለ? ደግሞስ ምን ያስፈራቸዋል? ያብራሩልኝ ” ብሎ ለጠየቃቸው ወ/ሮ ራቢያ አጥጋቢ መልስ ለመስጠት ሳይችሉ ቀርተዋል።
የኢህአዲግ/ወያኔ የጎሳ ፖለቲካ ሕዝቡን በአካል መለብለብ ከጀመረ ሰነበተ።ሺዎች የእዚህኛው ሌሎች የእዚያኛው ብሄር ተወላጅ ናችሁ እየተባሉ ተፈናቅለዋል።በተለይ ከአማራው ህዝብ ተወላጅ የሆኑ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ከጉርዳፈርዳ፣ከበንሻጉል፣ከኢልባቦር እና ከወለጋ አሰቃቂ ግድያ እና ድብደባ እየተፈፀመባቸው ለዘመናት ያፈሩትን ንብረት እየተነጠቁ መባረራቸውን ያመለከቱ ዘገባዎች ሲወጡ የነበረ መሆኑ ይታወቃል።

Martin Schibbye’s acceptance speech on behalf of Eskinder Nega

ARTICLE ID:

17885

Acceptance speech on behalf of Eskinder Nega, the World Association of Newspapers and News Publishers, Torino, Italy, 9 June 2014.   Ladies and gentlemen – members of the press. I really wish I did not have to do this. This morning, I thought, what if I get a phone call from Addis Abbeba and a cracked voice says: “Tafatchi! I am free. I will come and receive the Golden Pen myself”. It did not happen. A couple of hours ago, Eskinder Nega woke up to the shouting of “Kotera Kotera Kotera” from the loudspeakers, mixed with the police banging with their sticks on the walls of corrugated steel. Eskinder than stood, “Hulet, hulet”, “two and two” outside in a long line through the mud. When all 200 inmates in his room where accounted for, the door was locked again behind him. I am here on behalf of a colleague. And even though I am free from that very same prison, I will never be free from the memories, or the sounds. The first screams were always the worst, the frightened sound before the first stroke. Towards the end the abused prisoner was always silent. Six disease-ridden cells around a small yard with inmates coughing blood, overridden with lice, fleas and rats called ”Sheraton” by the inmates because, even if it was bad, the small dark cells where humans were kept like animals – standing chained in the dark, hanged upside town, and beaten until they confessed their made up crimes – were worse. The inmates named these cells “Hilton”. Humour is the last line of defence. But the worst thing with the federal police station Maekalawi, during this rainy summer month of July 2011, was not the methods, but rather who the Ethiopian Government had chosen to put there. In the cell to my right was journalist Wubshet Taye, in the cell in front of me was Reeyot Alemu. The fear of an Arabic Spring had led the Ethiopian regime to act rather than risk being acted upon. Journalists were charged as terrorists and the Arabic Spring turned into an early African Autumn. On the outside, one person stood up for all of us in our cells. One person dared to question the government’s ludicrous claim that we, the jailed journalists, were terrorists. One person said that the anti-terrorist law was used as a pretext to detain journalists, and was critical to the government Five days later, Eskinder Nega was arrested – and later sentenced to 18 years. His criticism of the law got him arrested, for violating the law. It was the sickest of jokes. I see this Golden Pen of his as an honour, not only for enduring more than 1000 days in jail – but above all for the journalism that led him to Kality. Eskinder Nega and his wife Serkalem Fasil’s contribution to bringing new blood into the Ethiopian media industry has been immense over the years. Together they showed what journalism could and should be, but too often isn’t. His articles were to the point provocative, they expanded the public sphere and signalled a new beginning that made it easier to breath for the readers. The couples’ newspapers have been instrumental for the development of journalism in Ethiopia. But he payed a price for the generations to come. The highest price. He both payed with his freedom. Looking back at his life we must remember that Eskinder Nega at many points faced a choice. He is intelligent, well educated, he could have chosen an easy life, he could have chosen another profession, but the love for the truth, for his country, for his fellow human beings, and for Ethiopia, made him into journalist. He stayed. And he continued to write. That decision brought him to the dark cells. Not one time. But nine. Nine. His stubbornness is demonstrating a brand of moral courage that we need now more than ever. And courage is the only thing he is guilty of. In Kality, at this time of the year, at the start of the rainy season it is burning hot in the daytime and freezing cold at night. The rooms are more like barns with concrete floors, and it is so crowded that you have to sleep on your side. Prisoners are packed likes slaves on a slaveship. Once a month an inmate leaves with his feet first. But, thinking back, the most difficult part in Kality was not the diseases or the torture. It was the fear of speaking. It’s not the guard towers with machine guns that keep the prison population calm. It is the geography of fear. People who speak politics are taken away. They disappear. This eats its way into your soul. I could wake up at night afraid I had said something negative about the government in my dream. It went under your skin. In such a situation, fearless people like Eskinder Nega help the whole prison population to keep their dignity. By still writing. Protesting. Not giving up. He helped us all maintain our humanity. But there is one thing I know that even Eskinder fears. That is to be forgotten. When you’re locked up as a prisoner of conscience, this is the greatest fear and the support from the outside is what keeps you going. This Golden Pen award will not set him free tomorrow, but it will ease his day today. He will go with his head high knowing that he is there for a good cause. That the pain and suffering has a meaning. That he is on the frontline in a fight that has turned global. And in that sense this Golden Pen is more important than food, medicine and water. It materialises the support and shows that he is not forgotten. That he is one of us. That an attack on one journalist is an attack on us all, and that jailing a journalist is a crime against humanity. To take a stand for Eskinder is also to take a stand for all those courageous journalists who should be here with us today in this room. But he is not only a symbol. He is also, and foremost, a human being of flesh and blood. He is a father, with a wife and a now an eight-year-old son. To demand his release is also to reunite a family that has suffered more in a mental prison over the years than any one should have to suffer. In a letter smuggled out to his eight-year-old son, Eskinder Nega wrote:  “ … The pain is almost physical. But in this plight of our family is embedded hope of a long suffering people. There is no greater honour. We must bear any pain, travel any distance, climb any mountain, cross any ocean to complete this journey to freedom. Anything less is impoverishment of our soul. God bless you, my son. You will always be in my prayers.” When I read these words by Eskinder I know that they will newer break him. Because he is in peace with himself. He knows that even though he is chained, robbed of his physical freedom, the freedom to talk or to be silent, the freedom to drink or eat, and even to shit. He knows, as do all prisoners of conscience, that you have it in you to keep the most valuable, the freedom that nobody can take from you, the freedom to determine who you want to be. Eskinder is a journalist. And every day he wakes up in Kality prison is just another day at the office. A couple of weeks ago the Ethiopian election campaign started with the jailing of nine more journalists. The crackdown was a flashing alarm to the world that no one is safe. That there is a hunting season for journalists in Addis Abeba. But despite this difficult situation there is light. Eskinder Nega’s courage has turned out to be contagious; a new generation is stepping up. A generation of young cheetahs have been taking enormous risks writing, Tweeting and speaking truth to power, demanding the jailed to be released. It is hopeful. It shows that they can jail journalists but they can never succeed in jailing journalism. Words led Eskinder Nega to Kality prison. And in the end it must also be words that set him free. When I see this Golden Pen of his, look back, and think of Eskinder who is left behind in the chaos, on the concrete floor, between walls of corrugated steel I feel sick to the stomach. But then I remember his smile and his strength and I think that at the end of the day, it’s not us that are fighting for his freedom – but rather he who is fighting for ours. Ayzoh Eskinder! Ayzoh! (translates: be strong, chin up). http://www.wan-ifra.org/articles/2014/06/09/martin-schibbye-s-acceptance-speech-on-behalf-of-eskinder-nega

Eritrea: Top Ten Source Countries for Refugees

Eritrean_TelAviv-690x350Khartoum (HAN) June 21, 2014 – Eritrea is in 10th place of the Source Countries for Refugees, accounting for 308,000 refugees. According to VOA, the United Nations Refugee Agency (UNHCR) says Somalia was among the world’s top three source countries for refugees last year. Photo: Eritrean refugees protest in front of the USA embassy, Tel Aviv .
In a Friday report marking World Refugee Day, the agency said Afghanistan, Syria and Somalia together accounted for more than half of the world’s 16.7 million refugees in 2013.
It said many of the 1.1 million Somalis who left the country sought refuge from conflict, drought and famine in neighboring Kenya and Ethiopia.
Sudan and the Democratic Republic of Congo also have relatively high rankings on the agency’s top 10 list of source countries, together accounting for more than a million refugees. People from both countries have been dealing with the impact of conflict.
Eritrea is in 10th place, accounting for 308,000 refugees. Isaias Afewerki says Eritrea exodus helps per capita income grow.
International media has reported over 4,000 Eritreans leaving the red sea nation every month as an “exodus” that could nearly wipeout most people out the country. However President Isaias told Eritrean tv that such reports are exaggerated. He mockingly suggested that even if such report is true, they are “not that bad” report since the exodus could “help raise our per capita income.”
President Isaias claimed that some “selfish” Eritreans are being attracted and lured by a better life in Europe and America, but they are not leaving because of oppression in his country. “If their excuse is really oppression in Eritrea, why don’t they stop and live in Sudan, Ethiopia or Kenya? But they continue their journey to Israel or Europe and America.” He said most Eritrean refugees are economic migrants, not victims of oppression or human rights abuse.
In a statement, U.N. High Commissioner for Refugees Antonio Guterres said that“peace is today dangerously in deficit.”
He also said the international community needs to overcome its differences and find solutions to the conflicts in “South Sudan, Syria, Central African Republic and elsewhere.”
The refugee agency says overall, more than 50 million people were forcibly displaced last year, an increase of about six million from the previous year.
Pakistan hosts the world’s largest number of refugees, more than 1.6. million. Kenya hosts the world’s largest number of Somali refugees and Ethiopia host the largest numbers of Eritrea, Somali and South Sudan in Africa.

Leave a Reply