March 29, 2016

(ሳምሶን ኃይሌ)

መግቢያ

እንደሚታወቀው ቄሳራውያን ኃይሎችና ኢትዮጵያውያኑ ጠባብ ብሄረተኞች ከሚጋሯቸው አጀንዳዎች ውስጥ ሁሉም በአማራ ሕዛብ ላይ መዝመታቸው ተጠቃሽ ነው፡፡ ቄሳራውያኑም ሆኑ ጠባብ ብሔርተኞች ቢቻሌ “ስለሕዝብ አንድነት ይሰብካል፤ ይዋጋል” የሚሉት የአማራ ሕዝብ ቢጠፋላቸው ካለዚያ ደግሞ ጠባቦች እንደሚሉት አከርካሪውን ተመትቶ አንገቱን ደፍቶ ቢኖርላቸው ይወዳሉ። ለዚህም ያለማቋረጥ ይሠራሉ። ፋሽስቶች ሕዝቡን በቋንቋና በሃይማኖት በመከፋፈል ሁሉም አማራውን በጠላትነት እንዲፈርጀውና እንዲወጋው ያደረጉት ጥረት ሙሉ በሙሉ ተሳክቷል ባይባልም ከፍተኛ ውጤት እንዳስገኘላቸው ግን ግልጽ ነው። በፋሽስቶች ከፋፍለህ-ግዛ ስትራቴጂ ምክንያት አገሩን ከወራሪው ኃይል ለመከላከል የዘመተው የኢትዮጵያ ሠራዊት ከትግራይና ራያ አካባቢ በወጡ ጠባብ ብሔረተኛና ጎጠኛ ኃይሎች ምን ያህል ጉዳት እንደደረሰበት ኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆኑ እንደነ አዶልፍ ፓርለሳክና ኮ/ሌ አልኸንድሮ ዴል ባዬ ያሉ የውጪ ዜጎች ሳይቀሩ ምስክርነታቸውን የሰጡበት ጉዳይ ነው።

በዚያ የግፍ ዘመን ኢትዮጵያውያን ጀግኖች የሚዋጉት ሁለት ዓይነት ጦርነት ነበር፤ ከፋሽስት ወራሪ ኃይልና ከአገር ውስጥ ጎጠኞችና ጠባቦች ጋር። ጦርነቱ በፋሽስቱ ኃይል አሸናፊነት መጠናቀቁን ተከትል ኢትዮጵያውያን ማዕከላቸውን ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ጎሬ ከተማ በማድረግ ጦርነቱን ለመቀጠል ወጥነው በሚንቀሳቀሱበት ወቅትም ቢሆን በጅማና አካባቢው የጠባብ ብሔረተኞች ጥቃት አልተለያቸውም ነበር።2 በአማራ ሕዛብ ላይ በጣሉያኖች የተጀመረው ዘመቻ በዘመናችን መልኩን ቀይሮና ተሻሽል በ”አማራው ገዥ መደብ” ስም ተግባራዊ በመደረግ ላይ ነው። ኦነጎች ለሥልጣን በበቁባት አጭር ጊዜ ውስጥ ከሕወሓትና ሻዕቢያ ጋር ተባብረው በዚህ ህዝብ ላይ በበደኖ፣ በአርሲ፣ በወለጋና በሌሎች አካባቢዎች የፈጸሙትን ዘግናኝ እልቂት ማንም ሊረሳው አይችልም። እነዚህ ጠባብ ብሔረተኛ ድርጅቶች “ነፍጠኛ፣ ትምክህተኛ” ወዘተ. እያሉ የሚወነጅሉት “ገዥ መደቡን ነው” ይበለ እንጂ ዓላማቸው ምንና በማን ላይ ያነጣጠረ እንደሆነ በጣም ግሌጽ ነው፡፡ ……. ( ሙሉውን ከዚህ ላይ ያንብቡ, pdf )

Source       Welkait.com

 

Leave a Reply