AUGUST 29, 2015
የሱዳን ገዳሪፍ ግዛት ሀገረ ገዢ ሜርጋኔ ሳሌህ በኢትዮጵያና በሰዳን መካከል አለ ብለው የሚያምኑት የረጅም ግዜ የድንበር ውዝግብ ይፈታ ዘንድ ድንበሩ እንዲካለል መጠየቃቸው ተሰማ፡፡ ሄራል ትርቢውን የተሰኘው ጋዜጣ ትላንት እንደዘገበው ሱዳን በምስራቃዊ ግዛቴ ገዳሪፍ ደቡብ ምስራቅ አል-ፍልሻጋ በተባለው አከባቢ ይገኛል የምትለውና የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች መሬታችው መሆኑን ሚናገሩለትን ይህን ምሬት ጉዳይ ከቀ/ጠ/ሚ/ አቶ/መለሰ ዜናዊ ግዜ ተጀምሮ እሳቸው ድንገት በመሞታቸው መቋረጡን ያስታውሳል ጋዜጣው፡፡ እናም አሁን ‹‹የኢትዮጵያና ሱዳን መንግስታት ድንበሩን እንደገና ለማካለል በተስማሙት መሰረት ይፈጸምና ድንበር ውዝግቡ ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ይፈታ››› ብለዋል ገዳሪፍ ሀገረ ገዢ፡፡
የሱዳኑ ሄራልድ ትርቢውን የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ‹‹ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ የኢትዮጵያን ምድር ለሱዳን አሳልፎ ትቶለታል በማላት ይከሳሉ›› ሲል ጋዜጣው ጽፏል፡፡ በባለፈው የፈረንጆች አመት ህዳር ወር የሱዳኑ አል-በሽርና የኢትዮጵያው ጠ/ሚ ሀይለማሪያም ደሳለኝ በቀ/ጠ/ሚ/ አቶ/መለሰ ዜናዊ ሞት የተነሳ የተቋረጠውን ድንበሩን እንደገና የማካለል ስራ የሚጀመርበትን አዲስ ቀን እንዲወስኑ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሮቻቸው መመሪያ ማስተላለፍቸውን ጋዜጣው ጠቅሷል፡፡
አዲስ ይደረጋል በተባለው ማካለል ጉዳይ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው መሬት 250 የ250 ካሬ ኪ.ሜ ነው ምናልባት የአዲስ አበባን ጠቅላላ ስፋት ከግማሽ በላይ የሚሆን መሬት ማለት ነው፡፡ በውስጡ ደግሞ ለእርሻ እጅግ ተስማሚ መሬት የሆነ 6 መቶ ሺ ሄክታር 6 መቶ ሺ የእግር ኳስ ሜዳ የሚያክል ለም መሬት አለው፡፡
የሱዳኑ ሄራልድ ትርቢውን እንደተነተነው ይህን ለም መሬት ደግሞ አጥባር ሲቲት ባዝላን የሰተሠኙ ወንዞች አቋርጠውት የሚያልፉ በመስኖ ሊለማና በአመት ሁለት ግዜ ሊመግብ የሚችል በጠራ ቋንቋ ጮማ መሬት ነው የሱዳን ገዳሪፍና ብሉ ናይል ግዛቶች ከአማራ ክልል ጋር የሚዋሰኑ ናቸው፡፡
ምንጭ ፤- አዋዜ