የ107 ፓርቲዎች ወግ! (በፍቃዱ ኃይሉ)

March 24, 2019 ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ 107 የፖለቲካ ድርጅቶች የሚመሩበትን «በፓርቲዎች መካከል የሚኖረውን ግንኙነት እንዲሁም በተናጠል የሚያደርጓቸውን እንቅስቃሴዎች የሚገዛ የአሠራር ሥርዓት ቃል ኪዳን» ፈርመዋል። ከቃል ኪዳኑ ይልቅ ዜና ሁኖ የሰነበተው እና ብዙ መቀለጃ የነበረው ግን «ኢትዮጵያ 107 የፖለቲካ ድርጅቶች አሏት» የሚለው ጉዳይ ነበር። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ 80 ሲባሉ የነበሩት ፓርቲዎች ባንድ ጊዜ ዘለው 107 […]

ስፍራህን አትልቀቅ! (ኤርሚያስ ለገሰ ዋቅጅራ)

March 24, 2019 ” አዲስአበቤ ወገብህን ጠበቅ አድርግ!” ኤርሚያስ ለገሰ ዋቅጅራ የጠቅላያችንን ማስፈራሪያ ከሰማሁ በኃላ ለሶስተኛ ጊዜ ገረብኩት። አሁንም ደጋግሜ አሳስባለሁ፣ ” አዲስአበቤ ከዛሬው የነገው የከፋ ነውና ለፍፁም ሰላማዊ ትግል ወገብህን ጠበቅ አድርግ!” https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=2536612373035182&id=100000593319208Filed in:Amharic

የቲም ለማ ቅቡልነት በብርሃን ፍጥነት እያሽቆለቆለ መምጣትና፣ የሃገራዊ ደህንነት ሥጋት!!! (ያሬድ ጥበቡ)

March 24, 2019 የቲም ለማ ቅቡልነት በብርሃን ፍጥነት እያሽቆለቆለ መምጣትና፣ የሃገራዊ ደህንነት ሥጋት!!! ያሬድ ጥበቡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአዲስ ወግ ስብሰባ መዝጊያ ላይ ያደረጉት ንግግር የሚደመጥ ነው። ብዙ ቁምነገሮችን አንስተዋል፣ የመጨረሻ ማሰሪያ ቃላቸውም በኢትዮጵያ ቀጣይነት ላይ መሆኑ ደስ የሚል ነው። ሆኖም ፣ ፓርቲያቸው ኦዴፓ በአዲስ አበባ ላይ የወሰደውን አቋም፣ በአዲስ አበባ ዙሪያ የሚያደርገውን ማፈናቀል፣ እርሳቸው በተገኙበት […]

ሎሬቱ ሰምቶ ይሆን? (መስፍን ማሞ ተሰማ)

March 24, 2019 ሎሬቱ ሰምቶ ይሆን? መስፍን ማሞ ተሰማ ሠላም ለናንተ ይሁን! ስለ ቴዎድሮስ ሹርባ ሎሬቱ ሰምቶ ይሆን? ከሰማ ንገሩን፤ ካልሰማም የምትችሉ ንገሩት፤ እኛ ግን ይህንን እንላለን። እነሆ ከ1868 እስከ 2019 (እአአ) በለንደን እንግሊዝ የኖረው የቴዎድሮስ ሹሩባ ሳይሆን የመይሳው መንፈስ ከመይሳው እናት ጋር አንድም ሁለትም እልፍም ሆነው ነው፤ ኢትዮጵያና ካሳ። በሹሩባው የገዘፈው ቴዎድሮስ ብቻ ሳይሆን […]

የ”ኬኛ” ፖለቲካ እንዴት ያሰልፋል? (መስከረም አበራ)

March 24, 2019 ኦህዴድ ወደ ስልጣን በመጣ ማግስት የሚያደርጋቸው ድርጊቶች “ኢትዮጵያዊነት ሱሴ ነው” ያስባለው የስልጣን ጥም አላማው የኦሮሞ የበላይነትን ማስፈን እንደሆነ የሚያስረዱ ናቸው፡፡የኦሮሞ የበላይነት ፖለቲካ ደግሞ ሊያሳካቸው ከሚፈልጋቸው ዋና ነገሮች አንዱ አዲስ አበባን የኦሮሚያ ግዛት እና የጨፌ ኦሮሚያ ግዛት ማድረግ ነው፡፡ በህገ-መንግስቱ የኦሮሚያ ግዛት አካልም ሆነ የጨፌ ኦሮሚያ ተዳዳሪ ያልሆነችውን አዲስ አበባን የኦሮሚያ ግዛት የማድረጉ […]

መንግሥት በየአካባቢው ቁጥራቸው እየተበራከቱ የመጡትን የጎበዝ አለቆችና ታጣቂዎችን በህግ አግባብ ሊያስታግሳቸው ይገባል – ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና

March 23, 2019 Source: https://mereja.com/amharic/v2/103259 “መንግስት ጊዜ በማራዘም ፖለቲካዊ ቀውሱን ሊወጣው እንደማይችለው ተገንዝቦ …በየአካባቢው ቁጥራቸው እየተበራከቱ የመጡትን የጎበዝ አለቆችና ታጣቂዎችን በህግ አግባብ ሊያስታግሳቸው ይገባል።” ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና (ኢ.ፕ.ድ) መንግሥት ጊዜ በማራዘም ፖለቲካዊ ቀውሱን ሊወጣው እንደማይችለው ተገንዝቦ በየአካባቢው ቁጥራቸው እየተበራከቱ የመጡትን የጎበዝ አለቆችና ታጣቂዎችን በህግ አግባብ ሊያስታግሳቸው ይገባል ሲሉ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና […]

“የተራራቀ ትውልድ” ፀጋዝአብ ለምለም ተስፋይ

N March 23, 2019 ኢኮኖሚክስ መምህርና ጸሓፊ (ሸክም የበዛበት ትውልድ፡ 2009 እና የምሥራቃዊት ኮከብ፡ 2010 መጻሕፍት አዘጋጅ) የሰው ልጅ እርስ በርሱ በማይነጣጠልና ሊነጣጠል በማይችል ባሕሪያዊና ጠባያዊ መገለጫዎች የተሳሰረ እንደኾነ ይታወቃል፡፡ የሰው ልጅ ከመሰሉ ጋር በሚያደርገው ተፈጥሯዊ ግንኙነት ይወለዳል፡፡ ይወልዳል፡፡ ይባዛል፡፡ አንደኛው ትውልድ ሌላኛውን ትውልድ እንደሚያፈራው ኹሉ እርሱም በተራው ሌላ ትውልድን ያፈራል፡፡ አንዱ ከሌላው ጋር እንደተሳሰረው […]

በዘረኝነት፣ በጥላቻና በመንጋ እየተናጠች ያለች ሀገር – (ከአብዱራህማን አህመዲን፤ የቀድሞ የፓርላማ አባል)

ዛሬ ሀገራችን “መስቀለኛ መንገድ ላይ ነው ያለቺው” የሚለውን ሃሳብ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ተደጋግሞ ሲነገር እሰማለሁ፡፡ በአባባሉ እኔም እስማማለሁ፡፡ እናም፤ ፋታ ወስደን፣ አውጥተን አውርደን፣ አመዛዝነን ቀጣዩን ጉዞ ካልጀመርን ልንወጣው የማንችለው አዘቅት ውስጥ የመዘፈቅ እጣ ፋንታ በእጃችን ላይ ነው። መደማመጥ ከቻልን እጣ ፋንታችን የተቃና እንዲሆን ማድረግ እንችላለን፡፡ በመጣንበት መንገድ የምንቀጥል ከሆነ ግን ሀገራችንንም ራሳችንንም አጥፍተን፣ ከወራት በኋላ […]

ቃለ ምልልስ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው – በወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ

በአለማየሁ አንበሴ የተጣፈ  • የትግራይና አማራ ህዝቦች ወደ ግጭት እንዲገቡ ማድረግ የለየለት እብደት ነው            • በቴሌቶኑ ኢትዮጵያዊ ፍቅርንና አንድነትን የሚያጎላ ድጋፍ ተደርጓል            • አዴፓ እና ኦዴፓ ሆድና ጀርባ ሆነዋል የሚባለው ምኞት ነው               ከ10 ዓመት በላይ የአማራ ክልላዊ መንግስትን ያስተዳደሩትና ከለውጡ መሪዎች አንዱ የነበሩት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፤ባለፈው የካቲት ወር መጨረሻ ላይ በፈቃዳቸው ሥልጣናቸውን መልቀቃቸው […]

ይሸሽበት ይጠጋበት ያጣ ትውልድ !!! (ውብሸት ሙላት)

March 23, 2019 ይሸሽበት ይጠጋበት ያጣ ትውልድ !!! ውብሸት ሙላት የኢትዮጵያ መንግሥታዊ ተቋማት እምነት የሚጣልባቸዉ፣ ተስፋ የሚደረግባቸዉ፣ የክፉ ቀን መጠለያና መጠጊያ የመሆን ቁመና የላቸዉም፡፡ ዜጎች ግጭትና መከራ ቢመጣብን ያድኑናል፣ያስጥሉናል ይተደጉናል የሚሏቸዉ ባጡ ጊዜ የጭንቅ ቀን ያወጣናል የሚሉትን መፍትሔ መፈለጋቸዉ አይቀሬ ነዉ፡፡ በኢትዮጵያ ፓርላማዉ ወይም የፌደሬሽን ምክር ቤት እንኳን ለዜጎች ዋስተና ሊሆን ይቀርና ራሳቸዉም በአስፈጻሚዉ ችሮታ […]