“የዘፈቀደ እስር” መቀጠሉ አሳሳቢ ሆኗል

June 8, 2024  “ስብስብ ለሰብዓዊ መብቶች ለኢትዮጵያ” መንግሥት በጋዜጠኞች፣ በኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ላይ ተጽዕኖ ፈጣሪ በኾኑ ሰዎች እና ፖለቲከኞች ላይ የሚፈጽመው “የዘፈቀደ እስር” እንዳሳሰበው ትናንት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ድርጅቱ፣ የመንግሥት ርምጃዎች የመገናኛ ብዙሃን ነጻነትን እና ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን የማፈን አዝማሚያን ያመለክታሉ ብሏል። መንግሥት “በሰብዓዊ መብቶች ላይ የሚፈጽማቸውን ጥሰቶች” እንዲያቆም እና የዜጎችን […]

ዶናልድ ትረምፕ ይታሰሩ ይሆን? የሕግ ባለሞያዎች ምን ይላሉ?

ጁን 08, 2024 ዶናልድ ትረምፕ ይታሰሩ ይሆን? የሕግ ባለሞያዎች ምን ይላሉ? የቀድሞ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2016ቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ፉክክር ወቅት፣ “ከተከፈለ የአፍ ማዘጊያ ገንዘብ ጋራ በተያያዘ የንግድ ድርጅታቸው ሰነዶች ላይ የማጭበርበር ወንጀል ፈጽመዋል” በሚል የጥፋተኝነት ውሳኔ ተሰጥቷቸዋል። በኒው ዮርክ ፍርድ ቤት የተሰየሙት ከሕዝብ የተውጣጡ ዳኞች በሰጡት ብይን የእስራት ቅጣት ውሳኔ […]

የአውሮጳ ህብረት የፓርላማ አባላት ምርጫ እና ከፊቱ የተጋረጠው ፈተና

June 8, 2024 – DW Amharic የአውሮጳ ህብረት 27 አባል አገሮች ከትናንት ሐሙስ ጀምሮ የፓርላማ ወኪሎቻቸውን እየመረጡ ነው። አራት ቀናት እንደሚወስድ በሚጠበቀው ምርጫው ከ370 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ለመምረጥ ተመዝግቧል። 720 የፓርላማ አባላት በሚመረጡበት ምርጫው ህብረቱ ከሩስያ ዩክሬን ጦርነት እና የስደተኞች ጉዳይ በምርጫው ላይ ተጽዖኖ ሳያሳድር አይቀርም ተብሏል።… … ሙሉውን ለማየት ወይም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

ሀገራዊ የምክክር ሂደት እና በጀርመን የኢትዮጵያውያን ስጋት

June 8, 2024 – DW Amharic  በኢትዮጵያ በተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ላይ ስጋት እንዳላቸው በጀርመን የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ተናገሩ፡፡ ኢትዮጵያውያኑ ለተሳካ የምክክር ሂደት እና ውጤት መንግስት ከታጠቁ ኃይሎች ጋር በገለልተኛ ሀገራት መነጋገርን ጨምሮ መፍትሄ ያሏቸውንም ሃሳቦች ጠቁመዋል፡፡… … ሙሉውን ለማየት ወይም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ