ከደብረ ጺዮን ወደ አክሱም ጺዮን | ክንፉ አሰፋ

መቀሌ ለደበቀቻቸው “ጀግኖች” ባለ ውለታ ናቸው። ከዚህም በላይ ይገባቸዋል የሚሉ አሉ። እምነት ለነሱ ኢምንት ነው። ሃይማኖት ደግሞ ፖለቲካ። ልብ ያለው ፈጣሪን ያስባል። ይሉኝታ ያለው አምላኩን ይፈራል። ህሊና ያለው ደግሞ የእግዚአብሄርን ስም ይጠራል። ይህ ሁሉ የሌለው ግን በባዶነቱ ዝም ብሎ ይቁነጠነጣል። ይህ አዲስ አይደለም። ራስ እንጂ ጭንቅላት ከሌለው ሰው ተቃራኒው ቢፈጸን ነበር የሚደንቀው። አንዱ ሰው ጓደኛውን […]

መንግሥት ሆይ ቁስልንና መንስኤን ለይ (ምሕረቱ ዘገዬ)

November 29, 2018 ሁሉም ሰው በግልጽ የሚረዳው በህክምናው ዓለም የሚተገበር አንድ አሠራር አለ፡፡ ይሄውም በአንድ ህመም ውጫዊ የስቃይ ምልክቶችና ውጤታቸው ላይ ብቻ ከማተኮርና የህመም ስሜቶችን ብቻ እየተከታተሉ ስቃይን በማስታገሻ መድሓኒቶች ለተወሰነ ጊዜ ፋታ ከመስጠት በተጓዳኝ የበሽታውን መንስኤ ማጥናትና ህመሙን ከሥር መሠረቱ አክሞ መፈወስ ተመራጭ የመሆኑ እውነታ ነው፡፡ ይህ አሠራር በጤናው ዘርፍ ብቻ የሚወሰን አይደለም፡፡ ጥረቴ […]

ነገረ-ወልቃይት – ክፍል ፪ (በመስከረም አበራ)

By Admin on November 30, 2018 (በመስከረም አበራ) ኅዳር 21 ፤ 2018 ዓ.ም. መስከረም አበራ የሃገራችን የፖለቲካ ችግር መሰረቱ የብሄረሰቦች ጭቆና እንደሆነ የሚያምነው ኢህአዴግ ለዚህ መፍትሄ ብሎ ያቀረበው ሃገሪቱን በዘውግ ፌደራሊዝም ከፍሎ ማስተዳደርን ነው፡፡እስከ መገንጠል የደረሰ የብሄረሰቦች መብት የሰጠው ህገ-መንግስት የዘውግ ፌደራሊዝምን ምርጫው አድርጓል፡፡ይህ የሆነው የሃገሪቱን ብሄረሰቦች ተከባብረው እንዲኖሩ የሚያስችል ስለሆነ ለሃገሪቱ ህልውና ሁነኛ መፍትሄ […]

እስኪነጋ (መስፍን ማሞ ተሰማ)

11/30/2018 እስኪነጋ መስፍን ማሞ ተሰማ ሠላም  ለናንተ ይሁን! አዎን እናምናለን። አዎን እየነጋ ነው። የህወሃትና ህወሃታውያን ዘመነ ፅልመት እየተገፈፈ ነው። በኢትዮጵያ ሠማይ ሥር የብሩህ ቀን አጥቢያ ፍካት ይታያል። ያለጥርጥር ይነጋል። አዲስም ቀን ይሆናል። ግን ገና አልነጋም። መቼ ይነጋል? ብላችሁ አትቸኩሉ። ንጋትም ተፈጥሯዊ ዑደቱን ያጠናቅቅ ዘንድ ግድ አለውና። ንጋቱ በህወሃትና ህወሃታውያን ፅልመት እንዳይጋረድ ግድ ነውና። ህወሃታውያን እነማን […]

የኤርትራ ህልም! (ጸሓፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ)

11/30/2018 የኤርትራ ህልም! ጸሓፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ ኤርትራ የአብረሃ ደቦጭ ሀገር! የሞገሥ አስገዶም ሀገር! የዘርዓይ ደረስ ሀገር! የሎሬንዞ ታዕዛዝ ሀገር! የደጃች ሀረጎት ሀገር! በአይበገሬ ጀግንነታቸው ድፍን አፍሪቃን ያኮሩ አርበኞች የበቀሉበት ምድር! —- ኤርትራ ድሮ ከእኛ ጋር ነበረች፡፡ አጼ ኃይለ ሥላሤ ለሁላችንም አስፈላጊ የነበረውን የፌዴሬሽን ፎርሙላ ሰረዙትና ህዝቡን አስቀየሙት፡፡ ደርግ ደግሞ የራሳችንን ህዝብ እንደ ባዕድ እየቆጠረ በመትረየስ […]

ህወሀት ሆይ በዚህ የጭንቅ ሰአት እንኳ እስኪ ልብ ግዢ – ወደ ህሊናሽ ተመለሽ?!? (ውብሸት ማናዬ)

11/30/2018 ህወሀት ሆይ በዚህ የጭንቅ ሰአት እንኳ እስኪ ልብ ግዢ – ወደ ህሊናሽ ተመለሽ?!? ውብሸት ማናዬ “የትግራይ ሕዝብ እየተደበደበ ነው።የትግራይ ሕዝብ ስጋት አለበት በየትኛው ሥፍራ።ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኛውም ክልል የመሥራትና ንብረት የማፍራት መብት በሕገ መንግሥቱ የተሰጠው መብት ነው” ይህች ጩህት ከጣራ በላይ መሰማት የጀመረችው  ዶ/ር አቢይ አህመድ ወደ ሥልጣን ከመጡና የሰው ልጅ እኩል ነው ማለትና ሌቦችንና […]

የኦሮምያው ፍጅት ምንጩ መቀሌ ነው!!! (ሀይል ገብርኤል አያሌው)

11/30/2018 የኦሮምያው ፍጅት ምንጩ መቀሌ ነው!!! ሀይል ገብርኤል አያሌው   አስገዳዮቹ ከሌላ ወገን ቢሆኑም ገዳይ ከራስ ብሄር ሲሆን ነገሮች ፈጥኖ የማለባበስና ገዳይም እኛ ሟችም እኛ ማንም አይስማብን አይነት የማለባበስ አካሄድ ለዜጎች ደህነትም ሆነ ለህግ የበላይነት አደገኛና አካሄድ መሆኑን መረዳት ይገባል!  በኦሮሚያ በወገኖቻችን ላይ በደረሰው ጭፍጨፉ ከልብ አዝነናል:: ከተራ ዜጎች አልፎ የጸጥታ አባላትን ጭምር ወደ ማጥቃት የተሸጋገረው […]

“ከሀገሬ አፈር የሚደባልቅ ቤልጅግ እና ጎራዴ ይዤ በሰጋር ፈረሴ ገስግሼ እወርድብሀለሁ!!!” (አምደ ጽዮን)

11/30/2018 “ከሀገሬ አፈር የሚደባልቅ ቤልጅግ እና ጎራዴ ይዤ በሰጋር ፈረሴ ገስግሼ እወርድብሀለሁ!!!” አምደ ጽዮን  * ደጃዝማች ኡመር ሠመትር(1871-1936)   ደጃች ዑመር ሰመተር በኦጋዴን ካልካዩ በተባለች ቦታ 1871 የተወለዱት ታላቁ ጀግና ደጃች ዑመር ሰመተር ለእናት አገራቸዉ ነፃነት ከወራሪዉ የፋሽስት ጦር ጋር ከተዋደቁት ጀግኖች አርበኞች አንዱ ናቸው። ፋሽስት ኢጣሊያ አገራችንን ለመዉረር የመጀመሪያዉን ጥይት የተኮሰችዉ በወልወሉ ግጭት ነበር። ነገሩ […]

ወደ ጎታቹ ፣ አግላዩና አሮጌው ስርአት አንመለስም! (ወሰን ሰገድ ገ/ኪዳን)

ወደ ጎታቹ ፣ አግላዩና አሮጌው ስርአት አንመለስም! (ወሰን ሰገድ ገ/ኪዳን) 11/30/2018 ወደ ጎታቹ ፣ አግላዩና አሮጌው ስርአት አንመለስም!   ወሰን ሰገድ ገ/ኪዳን   ወደ አለፈው ወደነቀዘው ሥርዓት አንመለስም! ወደ አግላይ ሥርዓት አንመለስም! አሳታፊ ሥርዓት ለመገንባት የምናደርገውን መውተርተር ለማጨናገፍ በሚፈጥሩት ሁከት ተስፋ አንቆርጥም!  ወደ ኋላ አንመለስም! ጉዞአችን ይቀጥላል፡- ወደፊት! ወደ አሳታፊ ሥርዓት! — ከአግላይ ወደ አሳታፊ […]

የተፎካካሪነት መለኪያው ምንድን ነው? (በበፍቃዱ ዘ. ኃይሉ)

November 30, 2018  የተፎካካሪነት መለኪያው ምንድን ነው? በበፍቃዱ ዘ. ኃይሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን “ተፎካካሪ” ብለን እንጠራቸዋለን ብለው ከተናገሩ በኋላ ብዙኃን መገናኛዎች እና ብዙዎቹ የፖለቲካ ድርጅቶች ሳይቀሩ ቃሉን ወርሰው እየተጠቀሙበት ነው፡፡ ይሁንና ተቃዋሚዎቻቸው የተፎካካሪነት ተክለ ቁመና ለማዳበር ሥማቸው ብቻ ሊበቃቸው አልቻለም፡፡ ባሳለፍነው ማክሰኞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፖለቲካ ድርጅቶቹ ጋር ያደረጉትን ውይይት ስመለከት የታሰበኝ ነገር […]